የማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል ዓመታዊ ጉባኤ ተካሔደ
• 20ኛ የምሥረታ በዓሉም ተከበረ
(ዴንቨር፣ ኮሎራዶ)፦ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከሉ በየዓመቱ የሚያካሒደው ጠቅላላ ጉባዔ የዚህ ዓመት ስብሰባ ግንቦት 18-19/2004 ዓ.ም በኮሎራዶ ግዛት የዴንቨር ከተማ ተካሔደ። በመላው አሜሪካ ከሚገኙ 11 ንዑሳን ማዕከላት (ቀጣና ማዕከላት) እና 2 ግንኙነት ጣቢያዎች የመጡ አባላት በተሰበሰቡበት በዚህ ጉባኤ ላይ ከዋናው ማዕከል የተወከሉ ሦስት ልዑካን፣ የካሊፎርኒያና የምዕራብ ስቴቶች ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት ኃ/ሥላሴ ዓለማየሁ፣ አበው ካህናት እና ተጋባዥ እንግዶች የተገኙ ሲሆን በዓመታዊ አገልግሎት ሪፖርትና ዕቅድ እንዲሁም በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሒዷል።