View in English alphabet 
 | Thursday, April 25, 2024 ..:: ዜናዎች ::.. Register  Login
ዜና

በእንዳለ ደምስስ

ስንክሳርንና ግብረ ሕማማትን እንዲሁም ሌሎችን መጻሕፍት ከግእዝ ወደ አማርኛ የተረጎሙት ታላቁ የመጻሕፍት ሊቅ ሊቀ መዘምራን ላእከ ማርያም ወልደ ኢየሱስ በተወለዱ በ90 ዓመታቸው ነሐሴ 1 ቀን 2004 ዓ.ም. በሞተ ስጋ ከዚህ ዓለም ተለዩ፡፡


ሊቀ መዘምራን ላእከ ማርያም ወልደ ኢየሱስ በአርሲ ክፍለ ሀገር በጢዮ ወረዳ ልዩ ስሙ ጨቢ አቦ በተባለ አካባቢ ከአባታቸው መምህር ወልደ ኢየሱስ ዘነበ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ወለተ ሩፋኤል ብስራት ነሐሴ 16 ቀን 1915 ዓ. ም. ተወለዱ፡፡

ከአባታቸው ከመምህር ወልደ ኢየሱስ ዘነበ ንባብ፤ ውዳሴ ማርያም ንባብና ዜማ ፤መዝሙረ ዳዊትና ግብረ ዲቁና በመማር ለስልጣነ ክህነት ከበቁ በኋላ በአካባቢያቸው በሚገኘው ዱግዳ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በዲቁና ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡

   ተጨማሪ ያንብቡ
  


ዜና

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

ብፁዕ ወቅዱስ ዶክተር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝደንት፣ የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዝዳንት ሥርዓተ ቀብራቸው ዛሬ ነሐሴ 17 ቀን 2004 ዓ.ም እኩለ ቀን ላይ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ከአኀት አብያተ ክርስቲያናትና ከሌሎችም የተወከሉ የእምነት አባቶች በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን በተገኙበት ተፈጽሟል፡፡
   ተጨማሪ ያንብቡ

  


ዜና



ዜና

የማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል ዓመታዊ ጉባኤ ተካሔደ

• 20ኛ የምሥረታ በዓሉም ተከበረ

(ዴንቨር፣ ኮሎራዶ)፦ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከሉ በየዓመቱ የሚያካሒደው ጠቅላላ ጉባዔ የዚህ ዓመት ስብሰባ ግንቦት 18-19/2004 ዓ.ም በኮሎራዶ ግዛት የዴንቨር ከተማ ተካሔደ። በመላው አሜሪካ ከሚገኙ 11 ንዑሳን ማዕከላት (ቀጣና ማዕከላት) እና 2 ግንኙነት ጣቢያዎች የመጡ አባላት በተሰበሰቡበት በዚህ ጉባኤ ላይ ከዋናው ማዕከል የተወከሉ ሦስት ልዑካን፣ የካሊፎርኒያና የምዕራብ ስቴቶች ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት ኃ/ሥላሴ ዓለማየሁ፣ አበው ካህናት እና ተጋባዥ እንግዶች የተገኙ ሲሆን በዓመታዊ አገልግሎት ሪፖርትና ዕቅድ እንዲሁም በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሒዷል።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና



Page 5 of 13First   Previous   1  2  3  4  [5]  6  7  8  9  10  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement