ምክሮች
ምክሮች - 1
• የሕይወት መገኛ የሆነውን አምላክህን እወቅ፡፡ በእርሱም ታመን፡፡ እርሱንም ተስፋ አምባና መጠጊያ በማድረግ ኑር፡፡
• ሕይወት ውጣ ውረድ የሚበዛባት ደስታና ሐዘን የሚፈራረቅባት መድረክ በመሆኗ ሁኔታዎችን እንዳመጣጣቸው በትእግሥትና በማስተዋል ለማሳለፍ ተጣጣር፡፡
• በሕይወት ዘመንህ በምታፈራው ገንዘብ የተራበን በማብላት የተጠማን በማጠጣት የታረዘን በማልበስና ችግረኞችን በመርዳት ጽድቅንና መልካም ስምን አትርፍበት፡፡
• ሕይወት በብቸኝነት እጅግ መራራ ናትና በጊዜ ከአምላክህ ጋር ተነጋግረህ የኑሮ ጓደኛህን በመምረጥ በመፈቃቀር በመተሳሰብና በመተጋገዝ ለመኖር ተዘጋጅ፡፡
nolink:
Written By: host
Date Posted: 12/23/2008
Number of Views: 10314
Return