View in English alphabet 
 | Wednesday, May 8, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
  

በሲያትል ቀጣና ማዕከል የተዘጋጀው ዐውደ ርዕይ ተጠናቀቀ

በብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የሰሜን ምዕራብ አሜሪካ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሚያዝያ 3 ቀን 2001 ዓ.ም. ተከፍቶ ለ2 ቀናት ለሕዝብ ሲታይ የቆየው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትናንት - ዛሬ - ነገ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ዐውደ ርዕይ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ በማኀበረ ቅዱሳን የሲያትል ቀጣና ማዕከል አስታወቀ፡፡ ብፁዕነታቸው በአውደ ርዕዩ የመዝጊያ ስነሥርዓት ላይ "ያየነው ዝግጅት በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ ተብሎ ለቤተክርስቲያን የተነገረውን ቃለ ትንቢት እየተፈጸመ መሆኑን ያስታውሰናል፡፡" በማለት የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡

 

 

ዐውደ ርዕዩን የሲያትል ከተማ ነዋሪዎች፣ ከፖርትላንድ ኦሪገንና ከካናዳ ቫንኮቨር በህብረት የመጡ ምእመናን እንዲሁም ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ዜጐች ተመልክተውታል፡፡ ከፖርትላንድና ከቫንኮቨር የመጡ ካህናትና ምእመናን ዝግጅቱ ለወደፊቱ በከተሞቻቸው እንዲታይ ሁኔታዎች እንዲመቻቹላቸው ጠይቀዋል፡፡

 

በአጠቃላይ የዐውደ ርዕዩ ይዘት ደረጃውን የጠበቀና የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን መጠነ ሰፊ መንፈሳዊ ሀብቶች፣ ወቅታዊ ሁኔታና የወደፊት ርዕይ በሚገባ ያመላከተ መሆኑ እንዳስደሰታቸዉ ከተመልካቾች ከተሰጠው አስተያየት ለመገንዘብ ተችል፡፡  

 

በዚህ ዐውደ ርዕይ ላይ በሲያትል ከተማ ከሚገኙ አድባራት የመጡ የሰ/ት/ቤት ወጣቶች በገለፃ ስላደረጉት ተሳትፎ እንዲሁም ምእመናንን በገንዘባቸው፣ በምክር፣ በፀሎትና በእውቀታቸው ስላደረጉት አስተዋጽኦ ቀጣና ማዕከሉ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡ፎቶዎችን ይመልከቱ


Written By: host
Date Posted: 4/12/2009
Number of Views: 8135

Return

  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement