View in English alphabet 
 | Friday, April 19, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
  

ነገረ ማርያም

 

ከመልአከ ሰላም ደጀኔ ሺፈራው
 «አልብኪ ነውር ወኢምንትኒ ላዕሌኪ፤»  መኃ 4:7

የትንቢተ ነቢያት ማረፊያ ፡-የስብከተ ሐዋርያት መነሻ.የሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምሥጢር ነገረ ማርያም ነው፡፡ ያለ ነገረ ማርያም ነገረ ክርስቶስን መናገር አይቻልም፡፡ በክርስትና ሃይማኖት ታሪክ የተነሡ አያሌ መናፍቃን የመጀመሪያ ችግራቸው የነገረ ማርያምን አማናዊ ትምህርት መቀበል ነበር ፡፡ ያም ችግራቸው ክርስቶስን በትክክል እንዳያምኑት አድርጓቸዋል፡፡ በነገረ ማርያም ላይ የተጣራ ትምህርትና እምነት ቢኖራቸው ኖሮ ለኑፋቄ አይጋለጡም ነበር ፡፡ ንስጥሮስ፡- «አምላክ ወልደ አምላክ» ብሎ በክርስቶስ ለማመን የተሳነው « ወላዲተ አምላክ . ወላዲተ ቃል. እመ እግዚአብሔር » ብሎ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ለማመን በመቸገሩ ነበር፡፡  PDF

ነገረ ማርያምን ከነገረ ክርስቶስ መለየት አይቻልም ፡፡ የተዋሐደ ነው ፡፡ ስለ እመቤታችን የሚነገረው ክፉም ሆነ በጎ ክርስቶስን ይነካዋል፡፡ የእግዚአብሔርን የማዳን ሥራ በምንናገርበት ጊዜ እመቤታችንን ወደ ጎን መተው አይቻልምና፡፡ ምክንያቱም ወልዳ ያስገኘች. አዝላ የተሰደደች. በማስተማር ጊዜው ከአገር አገር አብራው የተንከራተተች ናትና ፡፡ በተሰቀለበት ዕለትም ከእግረ መስቀሉ አልተለየችም፡፡ በአጠቃላይ አነጋገር ምክንያተ ድኂን አድርጓታል፡፡ 

ስለ ነገረ ድኅነት ስንናገር ጌታ ድኅነታችንን በመስቀል ላይ ፈጸመ የምንለው የዕለት ፅንስ ሆኖ በእመቤታችን ማኅፀን የጀመረውን ነው ፡፡ ሥጋውን ቆረሰልን .ደሙን አፈሰሰልን . ነፍሱን አሳልፎ ሰጠልን ብንል ከእርሷ የነሳውን ነው፡፡ ከእርሷ ነሥቶ በመስቀል ላይ የፈተተውን ሥጋውን እና ደሙንም የሕይወት ማዕድ አድርጎ ሰጥቶናል፡፡ መለኰታዊውን ፍህም በማኅፀን ከመሸከም ጀምሮ ይህ ታላቅ ምሥጢር የተፈጸመባት በመሆኑ መልዕልተ ፍጡራን መትሕተ ፈጣሪ ሆና ትመሰገናለች ፡፡ በመዝሙራችንም ሆነ በቅዳሴአችን ከስመ ሥላሴ ቀጥሎ የምንዘምረው የእመቤታችንን ምሥጋና ነው ፡፡ ቅዱስ ዳዊት ፡- « መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ፤ ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ . እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል፤ የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ. ስለ አንቺ የተነገረው ነገር ድንቅ ነው ፡፡» ያለው ለዚህ ነው ፡፡ መዝ 86.1-3 ፡፡ እርሷም እሳተ መለኰትን በማኅፀንዋ ተሸክማ ፡- « ሰውነቴ እግዚአብሔርን ታከብረዋለች ፡፡ ልቡናዬም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች ፡፡ የባርያውን ትሕትና ተመልክቷልና ፡፡ (ትንቢተ ኢሳያስን ተመልክቼ አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ከምትወልደው እመቤት ዘመን ቢያደርሰኝ ገረድ ሆኜ አገለግላታለሁ የሚለውን የልቤን አሳብ አይቷልና፡፡) እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብዕፅት ይሉኛል፡፡ ታላቅ ሥራን ሠርቶልኛልና ስሙም ቅዱስ ነው ፡፡ » ብላለች ፡፡ ሉቃ 1.46 ፡፡ ለእመቤታችን የተደረገላት ታላቅ ሥራ ፡- 1ኛ ከጥንተ አብሶ ነፃ ሆና መፈጠሯ ነው ፤ 2ኛ ፡- ከሀልዮ . ከነቢብ . ከገቢር ኃጢአት ነፃ መሆኗ   ነው ፤ 3ኛ ከልማደ አንስት ነፃ መሆኗ ነው ፤ 4ኛ ሰማይና ምድር የማይችሉትን . ኪሩቤል እሳታዊ መንበሩን የሚሸከሙለትን . ሱራፌል መንበሩን የሚያጥኑለትን . መላእክት የሚንቀጠቀጡለትን በማኅፀኗ መሸከሟ ነው፡፡ በመሆኑም እንደ ቅዱስ ዳዊት « ሀገረ እግዚአብሔር ድንግል ማርያም ሆይ ለአንቺ የተደረገው ነገር ዕፁብ ድንቅ ነው ፤» እያልን እናመሰግናታለን ፡፡

 
          እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ንጽሕት እምንጹሐን . ቅድስት እምቅዱሳን ናት ፡፡ ከተለዩ የተለየች. ከተከበሩ የተከበረች. ከተመረጡ የጠመረጠች ማለት ነው፡፡ ይኽውም እንደሌላው መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ስላልወደቀባት ነው፡፡ ይህም ይታወቅ ዘንድ ጠቢቡ ሰሎሞን « ለስእርተ ርእስከ. ለርእስኪ. ለገጽከ=. ለቀራንብትከ=. ለአዕይንትከ=. ለአእዛንኪ . ለመላትሕኪ ለአዕናፍኪ. ለከናፍርኪ. ለአፉከ=. ለአስናንኪ.  . . . ለክሣድኪ . . . ለአጥባትኪ፤ » እያለ መልክአ ማርያምን ማለትም የውስጥ የአፍአ ውበቷን ከማድነቅ ጋር « ወዳጄ ሆይ. ሁለንተናሽ ውብ ነወ<. ምንም ነውር የለብሽም ፤» ብሏታል ፡፡ መኃ. 4.7 ፡፡ ነውር የተባለውም መርገመ ሥጋን መርገመ ነፍስን ያመጣ የጥንት በደል (ጥንተ አብሶ) የሚባለው የአዳም ኃጢአት ነው፡፡
 
          እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅድመ ጸኒስና ቅድመ ወሊድ. ጊዜ ጸኒስና ጊዜ ወሊድ. ድኅረ ፀኒስና ድኅረ ወሊድ ድንግል እንደሆነች የታመነ ነው፡፡ ኢሳ 7.04 ፤ ሕዝ #4.1-4 ፡፡ ይህም ንጽሐ ሥጋን ንጽሐ ነፍስንና ንጽሐ ልቡናን አስተባብራ. አንድ አድርጋ ይዛ መገኘቷን ያረጋግጥልናል፡፡ በመሆኑም ጠቢቡ ፡- « ምንም ነውር የለብሽም ፤ » ሲል፡- የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ፡- « ደስ ያለሽ. ጸጋንም የተመላሽ ሆይ. ደስ ይበልሽ ፤ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነው ፤ ከሴቶች ተለይተሸ አንቺ የተባረክሽ ነሽ ፤ » ብሎ ከማብሠሩ በፊት. ባበሠራት ጊዘ?. ካበሠራትም በኋላ መሆኑን እንረዳለን፡፡ ሉቃ 1.!6 ፡፡ ምክንያቱም ፡- መልአኩ ገብርኤል ወደ አንዲት ድንግል ተላከ ፤ ይላልና ነው ፡፡ ይህም ድንጋሌ ሥጋን ብቻ ሳይሆን ድንጋሌ ነፍስንም የሚያመለክት ነው ፡፡ ድንጋሌ ነፍስን ገንዘብ ማድረጓም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጥንተ አብሶ የተያዘችበት ጊዜ ፈጽሞ እንዳልነበረ ያሳየናል፡፡ ጠቢቡም ፡- «ወዳጄ ሆይ. ሁለንተናሽ ውብ ነው ፤» ማለቱ ለዚህ ነውና ፡፡
 
 
« ዘርንባ ያስቀርልን ኖሮ፤ » ኢሳ1.9
 
ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ የነገረ ድኅነት ምሥጢር ተገልጦለት ያለፈውን ያለውን እና የሚመጣውን አገናዝቦ ሲናገር ፡- « የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ. እንደ ሰዶም በሆንን . እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር ፡፡ » ብሏል፡፡ ኢሳ 1.9 ፡፡ ይህም ለፍጻሜው ለእመቤታችን የተነገረ ትንቢት ነው ፡፡ ከዚህም በበለጠ ኹኔታ ትርጓሜ የማያሻው ደረቅ ትንቢት ሲናገረም፡- « ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ ድንግል ትፀንሳለች. ወልድንም ትወልዳለች. ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች ፡፡» ብሏል ኢሳ 7.04 ፡፡
 
          እነ ኢሳይያስ በጥንተ አብሶ ምክንያት ፡- « ሁላችን እንደ ርኵስ ሰው ሆነናል ፤ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው ፤ » ኢሳ %4.6፤ ቢሉም ፡- እግዚአብሔር ባወቀ ጥንተ አብሶ ፈጽሞ ባልደረሰባት በእመቤታችን ይመኩ. ተስፋም ያደርጉ ነበር ፡፡ ለዚህም ነው፡- « እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ . . . ፤ » ያሉት ፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከጥንተ አብሶ ገና ከጧቱ ንጽሕት ሆና የተዘጋጀች ጥንተ መድኃኒት ናትና ነው፡፡ ቅዱስ ኤፍሬምም ፡- « መመኪያ አክሊላች. ጥንተ መድኃኒታችን. የንጽሕናችን መሠረት ፤» እያለ ያመሰገናት ለዚህ ነው ፡፡
 
 
«በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር ነበር»
 
 
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓለም ከመፈጠሩ በፊት በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር ነበር ፡፡ ይህንንም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ « ዘእንበለ ይትፈጠር ሰማይ ወምድር. ወዘእንበለ ይሣረር ምድረ ገነƒ. ሀለወት ስብሕት ቅድስት ወቡርክት ይእቲ ማርያም. እንተ ተሰምየት ሰንበተ ክርስቲያን ፣ ጽዮን ፣ ቅድስት፣ እሞሙ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላእክት፡፡ የመላእክት እህታቸው፣ የሰማዕታት እናታቸው፣ ጽዮን ፣ ቅድስት፣ የክርስቲያን ሰንበት የተባለች. የተመሰገነች. በንጽሕና በድንግልና የተለየችና የተባረከች እርሷ ማርያም ሰማይና ምድር ሳይፈጠር የገነት ምድርም መሠረት ሳይጣል ነበረች፡፡ » ብሏል ፡፡ ዳግመኛም « በቤተልሔም ተወሊዶ መድኅን ክብረ ቅዱሳን . ፍስሐ ለኵሉ ዓለም. ወሠርዐ ሰንበተ ለሰብእ ዕረፍተ. ወይቤላ እግዚአብሔር ለማርያም ፡- አዝማንየ አዝማንከ=. አምጣንየ አምጣንኪ. ማርያም ሐቀፍኪዮ ወአነ ዮም ወለድኩዎ ፡፡ ለዓለሙ ኹሉ ደስታ የሚሆን የቅዱሳን ክብር መድኃኔዓለም በቤተልሔም ተወልዶ ፡- ለሰው ልጅ ዕረፍት ሰንበትን ሠራ. እግዚአብሔር ማርያምን ፡- ዘመኖቼ ዘመኖችሽ. መጠኖቼ መጠኖችሽ ናቸው ፤ እኔ ዛሬ ወለድኩት፡- ማርያም ሆይ አንቺ ታቀፍሺው ፡፡ » የሚል አለ ፡፡ ቅዱስ ያሬድ በድጓው እንደገለጠው እግዚአብሔር እመቤታችንን « ዘመኖቼ ዘመኖችሽ ናቸው ፤» ማለቱ ዓለም ከመፈጠሩ ዘመን ከመቆጠሩ በፊት በእርሱ ኅሊና መኖሯን የሚያስረዳ ነው፡፡ « መጠኖቼ መጠኖችሽ ናቸው ፤» ማለቱ ደግሞ እርሱ ቅድመ ዓለም አካላዊ ቃል ወልድን ያለ እናት ወልዶት አባት እንደሆነው እርሷም ድኅረ ዓለም አካላዊ ቃል ወልድን ያለ አባት ወልዳው እናት እንደሆነችው የሚያመለክት ነው ፡፡ ምሥጢራዊ መልእክቱም « ወላጆች ( አባትና እናት ) ለወለዱት ልጅ እኩል እንደሆኑ ሁሉ ወልድን በመውለድ በወላጅነት መሰልሽኝ ተስተካከልሺኝ ፤ » ሲላት ነው ፡፡ ይህም ፈጣሪን እና ፍጡርን የማነፃፀር የማስተካከል ሳይሆን የተሰጣትን ክብርና ልዕልና የማሳየት ነው፡፡ ለምሳሌ ጌታ ደቀመዛሙርቱን ፡- « እውነት እውነት እላችኋለሁ . በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል ፤ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል፡፡» ብሏቸዋል ፡፡ ዮሐ 14 .12 ፡፡ ይህም በማስተማርና ተአምራት በማድረግ እንደሚመስሉት ሲነግራቸው ነው ፡፡ «የሚበልጥ ያደርጋል፤» ማለቱም ፡፡ እርሱ ያስተማረው ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ነው፡፡ እነርሱ ግን ከዚህ በላይ ሃያ ሠላሳ ዓመት የሚያስተምሩ ስለሆነ ነው፡፡ እርሱ ለአብነት ሁለት ሦስት ሙት ቢያነሣ እነርሱ ደግሞ በስሙ ከዚያ በላይ ብዙ ስለሚያስነሡ ነው፡፡
 
 
 
«እመቤታችን በአዳም ባሕርይ ውስጥ»
 
 
          « ማርያምሰ ተኀቱ እምትካት ውስተ ከርሱ ለአዳም. ከመ ባሕርይ ጸአዳ፤እመቤታችን ማርያም ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች ፤ » ይላል ፡፡ ይህንንም በድጓው የተናገረው ቅዱስ ያሬድ ነው ፡፡ እመቤታችን በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ማብራቷ ከጥንተ አብሶ ነፃ ሆና መፈጠሯን የሚያመለክት ነው፡፡ አዳም ይኽንን ስለሚያውቅ ነው . እመቤታችንን ተስፋ ያደረገው ፡፡ ምክንያቱም በውስጡ እንደ ነጭ ዕንቁ ስታበራ ይታወቀው ነበርና ነው ፡፡ አባ ሕርያቆስ ይህ ምሥጢር ተገልጦለት « ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነበርሽ ፤» እያለ እመቤታችንን አመስግኗታል፡፡ ይህም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትእዛዝን በመተላለፍ በአዳም ላይ ከመጣ ጥንተ በደል በአምላካዊ ምሥጢር ተጠብቃ ከአዳም ወደ ሴት. ከሴት ወደ ኖኅ. ከኖኅ ወደ ሴም. ከሴም ወደ አብርሃም ስትቀዳ የኖረች ንጽሕት ዘር መሆኗን ያስረዳል ፡፡ ከላይ እንደተገለጠው ነቢዩ ኢሳይያስ « እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ » ያለው ይኽንን ነው ፡፡
 
 
« አንፂሖ ሥጋሃ ቀዲሶ ኪያሃ ኀደረ ላዕሌሃ»
 
 
ቅዱስ ያሬድ በሌላ አንቀጽ « ሥጋዋን አንጽቶ. እርሷን ቀድሶ. በእርሷ ላይ አደረ ፤» ብሏል፡፡ ይኽንን ንባብ በመያዝ ትርጓሜውንና ምሥጢሩን ቸል በማለት « ያነጻት የቀደሳት ከጥንተ አብሶ ነው ፤ » የሚሉ አሉ፡፡ ነገር ግን አይደለም፡፡ ጥንቱንም ንጽሕት ቅድስት አድርጐ በፈጠራት በእርሷ አደረ ማለት እንጂ ፡፡ « ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ፤ ( ለየ ) ፤ » እንዲል ፡፡ መዝ #5.4 ፡፡ ይህም ሁሉ ከተያዘበት ከጥንተ አብሶ ለይቶ ፈጠራት ማለት ነው፡፡ ጊዜው ሲደርስ ሥላሴ፡- አብ ለማጽናƒ. ወልድ ለለቢሰ ሥÒ. መንፈስ ቅዱስ ለማንፃት በማኅጸነ ድንግል አድረዋል፡፡ እዚህ ላይ « መንፈስ ቅዱስ ለማንፃት ፤» ማለቱ ፡- የመንፈስ ቅዱስ ግብሩ ማንፃት. መቀደስ መሆኑን ለመግለጥ እንጂ እድፍ ጉድፍ ኖሮባት አይደለም ፡፡ ለምሳሌ እግዚአብሔር የሰማይ ማደሪያውን ባለማለፍ ጸንታ የምትኖረውን እሳታዊ ዙፋን የተዘረጋባትን . ሰባት እሳታዊ መጋረጃዎች የተጋረዱባትን . ፀዋርያነ መንበሩ ኪሩቤልና ዐጠንተ መንበሩ ሱራፌል ያሉባትን ጽርሐ አርያምን ጥንቱኑ ንጽሕት ቅድስት አድርጐ ፈጥሯታል ፡፡ ቅዱስ ያሬድ ይኽንን ምሳሌዋ በማድረግ እመቤታችንን « ከሰማያት በላይ ያለ የአርያም የልዑል ሥፍራ ምትክ በምድር ላይ ከፍተኛ አርያምን ሆንሽ ፤ » ብሏታል ፡፡ በመሆኑም ያቺ ጥንቱኑ ንጽሕት ቅድስት ሆና እንደተፈጠረች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ጥንቱኑ ንጽሕት ቅድስት ሆና ተፈጥራለች እንጂ ኖራ ኖራ በኋላ የነፃች አይደለችም ፡፡ ለምሳሌ « ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው ፤» የሚል ገጸ ንባብ ይገኛል፡፡ መዝ )08.)# ፡፡ ይህም የእግዚአብሔር ቃል ልክ እንደ ቅቤ . እንደ ብረት ወይም እንደ ወርቅ ኖሮ ኖሮ የነጠረ ወይም ነጥሮ እድፍ ጉድፍ የወጣለት ነው አያሰኝም ፡፡ በመሆኑም እመቤታችንን በአባ ሕርያቆስ ምስጋና እግዚአብሔር አብ በሰማይ ሁኖ ምሥራቅንና ምዕራብን . ሰሜንና ደቡብን ዳርቻዎችንም ሁሉ በእውነት ተመለከተ ተነፈሰ አሸተተም. እንደ አንቺ ያለ አላገኘም፡፡ የአንቺን መዓዛ ወደÅ. ደም ግባትሽንም ወደÅ. የሚወደውንም ልጁንም ወደ አንቺ ሰደደ ፡፡ » እያልን ልናመሰግናት ይገባል፡፡ « እንደ አንቺ ያለ አላገኘም ፤» ማለቱም ፡- « እንደ አንቺ በጥንተ አብሶ ሳይያዝ የተገኘ የለም . ከአንቺ በቀር ሁሉ ተይዟል ፤ » ማለት ነው ፡፡
 
 
 
« ቀዳማዊ አዳም ወዳግማዊ አዳም »
 
 
          ቀዳማዊ አዳም የሚባለው ከምድር አፈር የተፈጠረው ሰው ነው ፡፡ « እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ከምድር አፈር ፈጠረው ፤ በፊቱም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት፤ ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው ሆነ ፡፡» እንዳለ ፡፡ ዘፍጥ 2.7 ፡፡ ዳግማዊ አዳም የተባለው ደግሞ በተለየ አካሉ ከሰማይ ወርዶ. በማኅጸነ ድንግል ማርያም አድሮ. ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷም ነፍስ ነስቶ በተዋሕዶ ሰው ሁኖ የተወለደው የባሕርይ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ይኽንንም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ፡- « አሁንም ክርስቶስ ከሞቱ ሰዎች ሁሉ አስቀድሞ ( በኵር ሆኖ ) ተነሥቷል ፡፡ በመጀመሪያው ሰው
( በቀዳማዊ አዳም ) ሞት መጥቷል. በሁለተኛው ሰው ( በዳግማዊ አዳም በክርስቶስ ) ትንሣኤ ሙታን ሆነ ፡፡ ሁሉ በአዳም እንደሚሞት እንዲሁ በክርስቶስ ሁሉ ሕያዋን ይሆናሉ፡፡ . . . መጽሐፍ እንዲህ ብሏል. የመጀመሪያው ሰው አዳም በነፍስ ሕያው ሆኖ ተፈጠረ ፤ ሁለተኛው አዳም ግን ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ነው ፡፡ ነገር ግን አስቀድሞ ሥጋዊው ቀጥሎም መንፈሳዊው ነው እንጂ መንፈሳዊው መጀመሪያ አይደለም ፡፡ የመጀመሪያው ሰው ከመሬት የተገኘ መሬታዊ ነው ፤ ሁለተኛው ሰው ከሰማይ የወረደ ሰማያዊ ነው፡፡ » በማለት ገልጦታል፡፡ 1ኛ ቆሮ 05.!-#5 ፡፡ ከዚህም የመጀመሪያው ፍጡር ሁለተኛው ፈጣሪ. የመጀመሪያው ከምድር ሁለተኛው ከሰማይ መሆኑን እንረዳለን ፡፡ እንግዲህ የሚያንሰው ቀዳማዊ አዳም ከመጀመሪያው ንጽሕት ከነበረች መሬት ተፈጠረ እያልን የሚበልጠውን ዳግማዊ አዳምን ከመጀመሪያው ንጽሕት ካልነበረች. በጥንተ አብሶ አድፋ ጐድፋ ከነበረች ከድንግል ማርያም ተወለደ ማለት ክርስቶስን ከአዳም ማሳነስ መሆኑን ማስተዋል ያስፈልጋል፡፡
 
 
«ብሥራተ ገብርኤል ወፅንሰት፡፡ »
 
 
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ተልኮ ወደ እመቤታችን በመጣ ጊዜ ፡- « ደስ ያለሽ. ጸጋንም የተመላሽ ሆይ. ደስ ይበልሽ ፤ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነው ፤ ከሴቶች ተለይተሸ አንቺ የተባረክሽ ነሽ ፡፡» በማለት አመስግኗታል፡፡ ሉቃ 1.!8 ፡፡ ከእርሷ በፊት ይህን በሚመስል ምስጋና የተመሰገነ ማንም አልነበረም ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ለእመቤታችን የተሰጠ ምስጋና ነው ፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጥንተ አብሶ ተይዛ ቢሆን ኖሮ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል « ጸጋን የተመላሽ ሆይ » አይላትም ነበር፡፡ ምክንያቱም ጥንተ አብሶ ጸጋዋን ጐዶሎ ያሰኝባት ነበርና ፡፡ ከላይ እንደገለጥነው እነ ኢሳይያስን ጽድቃቸውን የመርገም ጨርቅ ያሰኘባቸው ጥንተ አብሶ ነው፡፡ የቅድስናን ሥራ እየሠሩ « ሁላችንም እንደ ርኵስ ሰው ሆነናል ፤ » ያሰኛቸው ይኽው ነው ፡፡ ኢሳ %4.6 እነ ኤርምያስንም ፡- « ለሥጋ ለባሽ ሁሉ ሰላም የለም፡፡ ስንዴ ዘሩ እሾህንም አጨዱ ፤ » አሰኝቷቸዋል፡፡ ኤር 02. 03፡፡ እመቤታችን ግን ከመጀመሪያው ንጽሕት ቅድስት በመሆኗ « ጸጋን የተመላሽ ሆይ ፤ » ተብላለች፡፡
 
          አንዳንዶች፡- ለእመቤታችን ጥንተ አብሶ የጠፋላት መልአኩ ባበሠራት ጊዜ ነው ይላሉ፡፡ ይህም አባባላቸው ሁለት ጥያቄዎችን ያስነሣል፡፡ 1ኛ ፡- ከዚህ በፊት መልአክ ያበሠራቸው ማኑሄና ሚስቱ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ለምን ጥንተ አብሶ አልጠፋላቸውም; መሳ 03.2 ሉቃ 1.8 ፤ 2ኛ ፡- ጥንተ አብሶ የሚጠፋው በብሥራተ መልአክ ቢሆን ኖሮ አካላዊ ቃል ከሰማይ ወርዶ ከድንግል ማርያም ተወልዶ ሰው መሆን . መከራ መቀበልና በመስቀል ላይ መሞት ለምን አስፈለገው; በልዑል መንበሩ እንደተቀመጠ እልፍ አዕላፋት ወትእልፊተ አዕላፋት መላእክትን ልኮ በብሥራት ብቻ ጥንተ አብሶን አያጠፋም ነበር;
 
          አንዳንዶች ደግሞ « ጌታ በተፀነሰ ጊዜ በዚያ ቅጽበት ነው የጠፋላት ፤ » ይላሉ፡፡ ይህም ፡- «ጌታ የመጣው ጥንተ አብሶን እንዴት አድርጐ ለማጥፋት ነው; » የሚል ጥያቄ ያስነሣል ፡፡ መልሱም « በመስቀል ላይ በሚፈጽመው ቤዛነት በሚከፍለው መሥዋዕትነት ነው፤» የሚል ይሆናል ፡፡ እንግዲህ እመቤታችን ጥንተ አብሶ ነበረባት የሚሉ ከሆነ «እርሷም በጥንተ አብሶ እንደተያዙ እንደማናቸውም ሰው ናት፤ » ማለታቸው ነው፡፡ እንዲህ ከሆነ ደግሞ እንደማናቸውም ሰው በመስቀል ላይ በሚፈጸም ቤዛነት ብቻ ከጥንተ አብሶ ትድን ነበር እንጂ ተቃዋሚዎቹ እንደሚሉት ሊሆን አይችልም፡፡
 
 
 
« ሰው አይደለችም ወይ
 
 
ነቢዩ ኢሳይያስ ፡- « በትር ከእሴይ ሥር ትወጣለች. አበባም ከእርሷ ይወጣል፤» በማለት ስለ እመቤታችንም ስለ ጌታም ትንቢት ተናግሯል፡፡ ኢሳ 01.1 ፡፡ የበትር ምሳሌነት ለእመቤታችን ሲሆን የአበባ ምሳሌነት ደግሞ ለጌታ ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድም በዚህ ትንቢት ላይ ተመሥርቶ ፡- « ትወጽእ በትር እምሥርወ ዕሴይ. ወየዐርግ ጽገ@. ይእቲ በትር አምሳለ ማርያም ቅድስት ይእቲ. ወጽጌ ዘወጽአ እምኔሃ ፤ አምሳሉ ዘወልድ ዘኀደረ ላዕሌሃ. ቃል ሥጋ ኮነ ወተወልደ እምኔሃ፤ ከነገደ ዕሴይ በትር ትወጣለች. አበባም ከእሷ ይወጣል. ይህችውም በትር የማርያም አምሳል ናት ፤ ከእርሷ የሚወጣውም በትር የወልድ ምሳሌ ነው፤ የአብ አካላዊ ቃል በማኅጸኗ አድሮ ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷም ነፍስን ነሥቶ በተዋሕዶ ሰው ሁኖ ከእርሷ ተወለደ፤ » ብሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪም ቅዱስ ማቴዎስ እንደነገረን የእመቤታችን የዘር ሐረግ (የዘር ቅጂዋ) ከዕሴይ ወደ ዳዊት ወደ ሰሎሞን . ከዚያም ሲወርድ እስከ አልዓዛር .ከዓልዓዛር ደግሞ ሴት ልጁ ወደምትሆን ወደ ቅሥራ. ከቅሥራም ወደ ኢያቄም የደረሰ ነው፡፡ በእናቷ በኵል ደግሞ ከሊቀ ካህናቱ ከአሮን ወገን ናት፡፡ በመሆኑም ከሰው ወገን የተወለደች ሰው ናት፡፡
 
ካቶሊኮች፡- ጥንተ አብሶን የሸሹ መስሏቸው « ሰው አይደለችም . ኃይል አርያማዊት ናት » እያሉ ነው፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ይኽንን የካቶሊኮች አመለካከት የሸሹ መስሏቸው «እንደማናቸውም ሰው ጥንተ አብሶ የነበረባት ሰው ናት፡፡ » ይላሉ ፡፡ የሁለቱም « ከድጡ ወደ ማጡ » ነው ፡፡ የሁለተኛዎቹ አስተሳሰብ « ከሰው ወገን የተወለደች ሰው እስከሆነች ድረስ. የሰው ልጅ ተብላ እስከተጠራች ድረስ የግድ ጥንተ አብሶ ነበረባት ያሰኛል ፤ » የሚል ነው፡፡ ይህም አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ያስነሣል፡፡ ይኽውም ፡- « የሰው ወገን . የሰው ልጅ ለመባል የግድ የጥንተ አብሶ መኖር ያስፈልጋል ወይ; » የሚል ነው ፡፡ እንዲህስ ከሆነ ቀዳማዊ አዳም ከመበደሉ በፊት ለምን ሰው ተባለ; መርገመ ሥጋን መርገመ ነፍስን ያጠፋ ዳግማዊ አዳም ክርስቶስም ለምን የሰው ልጅ ተባለ; ያሰኛል፡፡ መናፍቃኑ እነደሚሉት ቢሆን ኖሮ፡- እነ ኢሳይያስ « እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ ፤» እያሉ አይመኩባትም ነበር፡፡ እነ ሰሎሞንም « አልብኪ ነውር » እያሉ አያመሰግኗትም ነበር፡፡ እነ ቅዱስ ኤፍሬም « አክሊለ ምክሕነ. ወጥንተ መድኃኒት. ወመሠረተ ንጽሕነ ፤ » እነ አባ ሕርያቆስም ፡- « ወኢረከበ ዘከማኪ፤ » አይሏትም ነበር፡፡ ስለዚህ ብርሃኑን ከጨለT. በጐውን ከክñ. ስንዴውን ከእንክርዳድ ለይተን አባቶቻችን ባቆዩልን ልንጸና ያስፈልጋል፡፡ ነገሩ የእውቀት ብቻ ሳይሆን የእምነት ነውና፡፡ የዕውቀት ሰዎች ሁለት ዓይነት ናቸው ፡፡ የመጀመሪያዎቹ እውቀታቸውን በትህትና ይዘው በእምነት የሚኖሩ ሲሆኑ ሁለተኛዎቹ ግን በእውቀታቸው ሲታበዩ በጥርጥር ማዕበል የሚመቱ . በኑፋቄ የሚለዩ . በክህደት የሚወድቁ ናቸው፡፡ ትእቢት ዲያቢሎስ የተያዘበት አሽክላ ነው፡፡ በንስሐ የማይመለሰው ለዚህ ነው፡፡ ዲያቢሎስ የትዕቢት እንጂ የእውቀትም የሥልጣንም ችግር አልነበረበትም፡፡ እነ አርዮስ. እነ ንስጥሮስ. እነ መቅዶንዮስም የትዕቢት እንጂ የእውቀት ችግር አልነበረባቸውም፡፡ ነገር ግን እውቀታቸውን ለክፋት ተጠቀሙበት ፡፡ እስከ ዓለም ፍጻሜ ለሚነሡ መናፍቃንም መጥፎ አብነት ሆኑበት፡፡ ስለዚህ ከዚህ እንዲሠውረን ተግተን ልንጸልይ ይገባናል፡፡ ለዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት . የንጽሕተ ንጹሐን . የቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን የድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን አሜን ፡፡

Written By: host
Date Posted: 10/23/2009
Number of Views: 11311

Return

  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement