View in English alphabet 
 | Thursday, April 25, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
  

የውዳሴ ማርያምና ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ በኮንፈረንስ ስልክ

የውዳሴ ማርያምና ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ በኮንፈረንስ ስልክ


“እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤ ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጎአልና፤ ስሙም ቅዱስ ነው::” ሉቃ 1፡48-49


ለተወደዳችሁ አባቶች፡ እናቶች ወንድሞችና እህቶች፡ በሙሉ :
የእግዚአብሔር ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን!

የማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማዕከል የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል በየዓመቱ ነሐሴ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የፍልሰታ ጾም በሊቃውንተ ቤ/ክን አባቶች አማካኝነት የእመቤታችንን ውዳሴና ቅዳሴ ትርጓሜ ሲያቀርብ ቆይቷል። ዘንድሮም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ከዋዜማው ማክሰኞ ሐምሌ 30 2005 ዓም አንስቶ ይጀምራል።

ስለዚህ እርስዎም በሰዓቱ በስልክ ጉባኤው ላይ በመሳተፍ ነፍስዎን ቃለ እግዚአብሔር ይመግቡዋት፡ ከወላዲተ አምላክ ውዳሴና ቅዳሴ ይሳተፉ፡ ስለሀገር፡ ወገንና ስለቅድስት ቤ/ክንዎ በጋራ ይጸልዩ። ሌሎች ወንድሞችና እህቶችም እንዲገኙ ይጋብዙ።

ቀናት፡ ከማክሰኞ ሐምሌ 30 - ረቡዕ ነሐሴ 15 ቀን 2005 ዓ.ም/ August 6-21, 2013
ሰዓት፡ ከምሽቱ 9:00 PM - 10:00 PM PST(ሲያትል ሰዓት)
12፡00AM - 1:00AM EST (ዲሲ ሰዓት)
የኮንፈረንስ ቁጥር፦ 1-559-726-1200     መግቢያ ኮድ፦ 24-81-12


ማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማዕከል የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎትክፍል

ወስብሐት ለእግዚአብሔር


Written By: host
Date Posted: 8/6/2013
Number of Views: 4735

Return

  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement