View in English alphabet 
 | Thursday, March 28, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
  

የምንፈልገው ኦርቶዶክሳዊ ወጣት

ከብፁዕ አቡነ ሙሳ
(የግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተ ክርስቲያን የወጣቶች ጉዳይ ጳጳስ)

በለብ ለብ ክርስቲያንና በኦርቶዶሳዊ ክርስቲያን መካከል ትልቅ ልዩነት አለ ምክንያቱም ኦርቶዶክስ ማለት ርቱዕ በሃይማኖቱ ርቱዕ በምግባሩ ነውና።

ኦርቶዶክስ የሚለው ቃል የግሪክ ሲሆን ኦርቶ”  ማለት የቀና የተስተካከለ ርቱዕ ማለት ሲሆን፤ ዶክስማለት ደግሞ ሃይማኖት ማለት ነው። ኦርቶዶክስ ማለትም የቀና  የተስተካከለ ርቱዕ የሆነ ሃይማኖት ማለት ነው።

 

1. ርቱዕ በሃይማኖቱ

የኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖታችንን ልዩ የሚያደርጓት የእምነት ባሕርያት አሏት።

. የተረዳች ናት

    ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በትምሕርተ ሃይማኖቷ በቀኖናዋ እና በትውፊቷ እንከን አይገኝባትም ምክንያቱም ሐዋርያት በቃልም በጽሑፍም ያስተማሩትን በሙሉ ይዛለችና። 2 ተሰ. 215  ይኸም ዘመኑ የግንጥል ጌጥን ትምህርት ይዞ ለሚያነሳቸው ምሥጢረ  ሥጋዌ ፣ ምሥጢረ ሥላሴ፣ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣ የምልጃ  ትምህርት፣ አጽዋማት፣ በዓላትንና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች በበቂ ሁኔታ ለመመለስ አስችሏታል።

    . ርትዕት ናት

    ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሐዋሪያዊት የሆነች ያልተበረዘች ያልተከለሰች  ያልወየበች ያልተጨመረባት ያልተቀነሰላት ወደ ግራም ሆነ ወደ ቀኝም ልክ ለኢያሱ እንደተነገረው ( ኢያ. 17) ያላለች ርትዕት ቀጥተኛ ሃይማኖት ነች። አንዳንዶች ጭልጥ ብለው ሲክዱ ሌሎች ደግሞ እውነተኛውን መንገድ ለቀው በመሰላቸው ሰውኛ ፍልስፍና  ሲመሩ እርሷ ግን ሐዋርያት እንደተከተሏት ሳትዛነፍ በቅብብል (Apostolic Succession)  ከእኛ ደርሳለች። ሁለቱም ወገኖች ዛሬ ቢያስቡበትና ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ተመልሰው ልብ ቢሉ ያለምንም ጥርጥር ወደ ኦርቶዶክስ ሃይማኖታቸው  በተመለሱ ነበር።

    ምልዕት ናት

    ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖት አንዱን ጥላ አንዱን አንጠልጥላ አትሄድም ስለ እምነት ስታስተምር ምግባርን አስተባብራ  ነው። ያዕ 226 ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስታስተምር የእናቱን የቅድስት ድንግል ማርያምን፣ የወዳጆቹን የሐዋርያትን፣ የጻድቃን እና የሰማዕታትን፣ የቅዱሳን መላእክትን ክብር እና ምልጃ ሳትዘነጋ  ነው። ልጆቿ ቅዱሳት መጽሐፍትን እንዲማሩ ስታደርግ በራሳቸው ፈቃድ ሐረግ እየመዘዙ ሳይሰነጥቁ አባቶቻቸው ሐዋሪያት ብሎም ከነርሱ በኋላ መንገዳቸውን የተከተሉ አበው ያስተማሩትን በመያዝ ነው። ምክንያቱም እኛ ክርስትናን ተቀበልነው እንጂ አልጀመርነውምና የቀደሙትን ማየት ያስፈልጋል።

ኤር 616ስለዚህ በመንገዱ መጓዝ እንጂ አዲስ ፈር አናወጣም። ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሥልጣነ ክህነት ስትሰጥ ምእመናን በቤተ ክርስቲያን ያላቸውን ተሳትፎ ሳትንቅና የቤተ ክርስቲያን አካል መሆናቸውን እያስተማረች ነው።

ስለዚህ ኦርቶዶክሳዊት እምነታችን ምግባር ከሃይማኖት እንደ ዘይትና ክር አዋሕዳ የምታስተምር ናት።

    መጽሐፍ ቅዱሳዊት ናት

    ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለቀኖናና ለትውፊት ታላቅ ቦታ ትሰጣለች። ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ ራሱን ያገኘችው በትውፊት ከአባቶች በመቀበል ነውናይሁን እንጂ የቤተ ክርስቲያናችን ትምህርተ ሃይማኖትም ሆነ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን መሠረቱ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ያሉት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች በመንፈስ ላነበባቸው ስለ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ፣ ምሥጢረ ሥላሴ፣ ስለ ምልጃ ትምህርት፣ ታቦት እና ቤተ መቅደስ ትምህርቷ እውነተኛነት ይመሰክራሉ።

2ርቱዕ በምግባር

የኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖት ልጆች ልዩ የሆነ የምግባር ባሕርይ አለን።

የግል ጸሎት

    ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ በጸሎት ከአምላካቸው ጋር መገናኘት አለባቸው። አንኳኩ ይከፈትላችኋል ተብሏል እና ማቴ77 ስለዚህ በቀን የተወሰነ ሰዓት መድቦ ስለ ራሱ፣ ስለ ሀገሩ፣ ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ዕለት ሥራው፣ ወዘተ 。。 መጸለይ አለበት። ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ ካስተማረን አቡነ ዘበሰማያት ጀምሮ የአበው የመንፈስ ፍሬ የሆኑትን የጸሎት መጽሐፍት፣ መዝሙረ ዳዊትን እና ሌሎችንም ይጨምራል።ዕብ 117

የማኅበር ጸሎት

    አባቶቻችን ሐዋርያት በኅብረት ሆነው ለጸሎት ይተጉ እንደነበረው የሐዋ82በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን የምእመናን አንድነት እንዲኖር ጸሎተ ምሕላ፣ ጸሎተ ኪዳን፣ ሰዓታትና ማኅሌትን በመሳሰሉት የአንድነት ጸሎተ ሥርዓቶች መካፈል አለብን።

መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ

    በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ለቅዳሴም ሆነ ለምሥጋና ሰዓት ለዕለት ተዕለት የክርስቲያኖች የወንጌል ምግብነት ያመች ዘንድ መጽሐፍ ግጻዌ የመጽሐፍ ቅዱስ የዕለት ምግብ ተዘጋጅቷል። ለምክር፣ ለተግሳጽ፣ ልብንም ለማቅናት፣ በየዕለቱ  መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ይገባል። የዕለት ምግባችንን ስጠን ዛሬ የሚለው ጸሎት የሚያመለክተው እንጀራችንን ብቻ አይደለምና።

ድርሳናትን ማንበብ

    የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው ምሳ 107፤ በተባለው መሠረት ቅዱሳንን በተለያየ መንገድ ታስባቸዋለች፤ ስለ በረከታቸውም ታከብራቸዋለች። ከዚህም አንዱ ገድላቸውን፣ ተአምራታቸውን ጽፋ ለትውልድ ማውረሷ ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የብሉይ ኪዳን አበውን እየጠቀሰ በዕብራዊያን 11 ላይ የእምነት ምሥክር እንዳደረጋቸው ሁሉ ይኼው ትውልድ የቅዱሳን አባቶችን ታሪክ ገድልና ምክር በማንበብ መማር አለበት።

ማስቀደስ እና መቁረብ

    ጸሎተ ቅዳሴ በውስጡ 3 ነገሮችን ይዞአል። የነገረ መለኮት ትምህርት፣  ጸሎት እና  ቅዱስ ቁርባን ናቸው። ይኸውም በምሥራቃውያን ኦርየንታል ቸርችስየመንፋሳዊ ዜማ ልህይ Melody)   የሚቀርብ ነው።ኦርቶዶክሳዊ የሆነ ክርስቲያን በዚህ ጸሎተ ቅዳሴ ላይ መገኘት አለበት። ቅዳሴው ይበል ካህን፤ ይበል ዲያቆንእንደሚለው ሁሉ ይበል ሕዝብምይላልና በዚህ ሰዓት ተገኝቶ  ትምህርቱን መማር የጸሎቱ ሙሉ ተካፋይ መሆን በመጨረሻም ሥጋወደሙን መቀበል ይገባዋል።

መጾም

በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሁለት ዓይነት አጽዋማት ይገኛሉ። የአዋጅ አጽዋማትኢዮ 114

  1. ረቡዕና ዓርብ፣
  1. የሐዋርያት፣
  1. የነቢያት፣
  2. ዐብይ ጾም፣
  3. ጾመ ፍልሰታ፣
  4. ጾመ ነነዌ፣
  5. ጾመ ገሃድ፣

እነዚህ አጽዋማት ከአባቶቻችን የወረስናቸው የኑሮ ፍሬዎች ሲሆኑ የእናታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን መከራዋን እያሰብን ፍቅራችንን የምንገልጽበት በሐዋርያት፣ በነቢያት፣ በጻድቃንና በሰማዕታት ፈለግ ለመሄድ እግዚአብሔርን እየጠየቅን ሕይወታቸውን የምንኖርበት የጌታችን የመድኃኒታችንን  ስቃዩን፣ መከራውን ለኛ ሲል የሠራልንን የፍቅሩን መግለጫ ሞቱን የምናስብበት ወቅት ነው።

    የግል አጽዋማትም በፈቃድ ለጸጋ የሚደረጉና በምክረ ካህን፣ በትዕዛዘ ካህን ለንስሐ የሚደረጉትን ያጠቃልላል። እነዚህም የኃጢአት መሠረት የሆነውን ዲያቢሎስን ለመዋጋት  የሚደረጉ ናቸውማቴ1721  ሉቃ 236-38 የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ልጆች በመጽሐፍ ቅዱስ ሕግ በአባቶቻችን ሥርዓት እንደሚገባ መጾም ያስፈልጋል።

ለቤተ ክርስቲያን በዓል ላይ መሣተፍ

     ሰሞነ ሕማማትን በመሰሉ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጸሎት፣ በጾምና በስግደት ቅዱሳን መጽሐፍትን በማንበብና በመዘመር በሚዋልባቸው መንፈሳዊ ሰሞናት የውጭ ተመልካች ሳይሆኑ ከበረከቱ መካፈል።

ምክረ አበውን መቀበል

    የቀደሙ አባቶች በመንፈሳዊ ጉዞ ብዙ ጸጋ አግኝተውበታልና፥ከቃላቸውና ከሕይወታቸው ወጣቱ ብዙ ይማራል። ስለዚህ ሊቃውንትና  ካህናትን ቀርቦ  መንፈሳዊ ምክራቸውን ተጋድሎዋቸውንና ትምህርታቸውን መማር ያስፈልጋል። ጢሞቴዎስ ያደገው በጳውሎስ ምክር ነው። ለጢሞቴዎስ የተላከው መልእክት ጳውሎስ በመንፈስ በተጓዘበት ጎዳና ያገኘውን ትምህርት ለልጁ ያካፈለበት ነው።

    በዚህ ዓይነት መንገድ አባቶች ካወጡት ሥርዓት ጋር አንድ ሆነን በእምነትም በምግባርም ኦርቶዶክሳውያን መሆን እንችላለን፣ በዚህም እግዚአብሔርን እያከበርን በፍቅሩ እቅፍ ውስጥ እንገባለን ነገር ግን በጭፍን ሞራል fanaticism) አይደለንም። ሁሉንም በፍቅር እንቀርባለን ነገር ግን ከእምነታችንና ሥርዓታችን እንዲሁም ትውፊታችን ለሰው ስንል የምንተወው አሊያም የምንለውጠው አይኖረንም ።   

                                       ምንጭ፡-  ሐመር ጥር 1986 /


Written By: useducation
Date Posted: 3/6/2016
Number of Views: 9997

Return

  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement