View in English alphabet 
 | Thursday, April 25, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
አማርኛ




ላክ   ተወው
ኅብረ ነገር

 
“እምነ ጽዮን ይብል ሰብእ ወብእሲ ተወልደ በውስቴታ ወውእቱ ልዑል ሣረራ"
  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

ትንሣኤ (በመልአከ ሰላም ቀሲስ ያሬድ ገ/መድኅን)

በአርዓያ ሥላሴ የተፈጠረው አዳም

አጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ ፍጥረታትን ለተከታታይ አምስት ቀናት ከፈጠሩ በኋላ በስድስተኛው ቀን /ዓርብ/ በነግህ እንዲህ አሉ።  ‹‹ንግበር ሰብአ በአርዓያነ ወበአምሳሊነ፤ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር›› /ዘፍ ፩፥፳፮/።  ሥላሴ በመልካችን እንደ ምሳሌያችን ማለታቸው እንዴት ነው ቢሉ ሥላሴ ለባውያን፣  ነባብያን፣  ሕያዋን ናቸው።  አዳምም ለባዊ፣  ነባቢ፣  ሕያው ነው።  ሥላሴ ፍጹም መልክእ እንዳላቸው አዳምም ፍጹም መልክእ  አለው።  ሥላሴ በልብ በቃል፣  በእስትንፋስ ይመሰላሉ ለሰውም ልብ፣  ቃል፣  እስትንፋስ አለው። ሥላሴ በባሕርያቸው የሚገዙትን አዳም በጸጋ እንዲገዛ ሥልጣን ሰጥተውታል።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

ቆሮንቶስ የግሪክ ከተማ ናት። ከአቴናም 75 ኪ.ሜ. ያህል ትርቃለች። በአዲስ ኪዳን ዘመን ስድስት መቶ ሺህ ሰዎች የሚኖሩባት ትልቅ ከተማ ነበረች። አቀማመጧ በሁለቱ የግሪክ አውራጃዎች በመቄዶንያና በአካይያ መካከል በሚገኘው ልሳነ ምድር ነበረ።

ከተማይቱ የተመሠረተችው በባሕር መገናኛ ላይ በመሆኑ ከምሥራቅና ከምዕራብ ለሚመጡ መርከቦች ምቹ ወደብ ነበረች። ከዚህም የተነሣ ንግድ እየደራባት ሄደ። ከተማይቱም እጅግ ተለወጠች። የከተማይቱ ነዋሪዎች የሚያመልኩት አፍሮዳይቲ የምትባለዋን የፍቅር አምላክ ነበር። «ቆሮንቶሳዊ» መባል የስድብ ስም እስኪሆን ድረስ የዝሙት ኃጢአት በከተማይቱ በዛ። አብዛኛዎቹ ነዋሪዎች ግሪኮች ሲሆኑ ብዙ ሮማውያንና አይሁዶች ይኖሩባት ነበር።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሚገኘው የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን በመቃጠሉ መነሾ በሰሜን አሜሪካ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት ሦስቱ ማኅበራት ማለትም በማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል፣ በሰሜን አሜሪካ አህጉረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ እና ማኅበረ በዓለ ወልድ ባደረጉት ጥሪ እጅግ አስደሳች ምላሽ መገኘቱን በዚህም እስካሁን በጠቅላላው $24,206.52 ዶላር መዋጣቱን የማኅበራቱ ኃላፊዎች ገለፁ።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

ማንም ሲፈተን በእግዚአብሔር እፈተናለሁ አይበል
/በቀሲስ ዶ/ር መስፍን ተገኝ/

  


Page 17 of 41First   Previous   12  13  14  15  16  [17]  18  19  20  21  Next   Last   

 የ10 ዓመት የስብከተ ወንጌል ማስፋፋፊያ ፕሮጀክት Minimize

ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት እና ለመርዳት ይህንን ይጫኑ።


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ሶሻል ኔትወርኪንግ

Share |

  
 ግጻዌ


  
 የተላለፉ የቴሌቪዥን እና ሬዲዮ መርሃ ግብር ለመከታተል Minimize


  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement