View in English alphabet 
 | Tuesday, April 23, 2024 ..:: ትምህርተ ሃይማኖት ::.. Register  Login
ትምህርተ ሃይማኖት

ወልድ ዋሕድ /ክፍል ፫/


በሊቀ ካህናት ኃይለሥላሴ ዓለማየሁ ደስታ


እግዚአብሔር ዘለዓለማዊ ነው

ዘለዓለማዊ የሚለው ቃል ከቋንቋነቱ አኳያ ሲታይ የእግዚአብሔርን ባሕርይ ለመግለጽ ደካማ ወይም አናሳ ቃል ሆኖ የሚታይ ይመስላል። በእርግጥም የቃሉ ገላጭነት የደከመ ወይም የጠበበ ነው። ይሁንና ሌሎች ቃላት ቢሆኑም የእግዚአብሔርን መለኮታዊ ባሕርይ በፍጹምነት የመግለጽ ብቃት አላቸው ብሎ መገመት አስቸጋሪ መሆኑ አይቀርም።

የሆነ ሆኖ ግን ዘለዓለማዊ ከሚለው ቃል መረዳት የሚቻለው፣ እግዚአብሔር አምላክ ቅድመ ዓለም የነበረ፣ በማዕከለ ዓለም ያለ፣ ዓለምን አሳልፎ የሚኖር፣ ፍጻሜ /መጨረሻ/ መነሻና መድረሻ የሌለው፣ እርሱ ራሱ መጀመሪያና መጨረሻ፣ የሆነ፣ የነበረ፣ ያለና የሚኖር ኅልፈትና ሽረት የሌለበት አምላክ መሆኑን ነው።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

ወልድ ዋሕድ /ክፍል ፪/

በሊቀ ካህናት ኃይለሥላሴ ዓለማየሁ ደስታ


እግዚአብሔር ፈጣሪ ነው

ፈጣሪ ስንል የሌለን ወይም ያልነበረን ነገር በሥልጣኑና በከሃሊነቱ ያስገኘ፣ ዓለምን እምሀበአልቦ /ካለመኖር ወደ መኖር/ የፈጠረ ማለታችን ነው። ዓለምን እምሀበአልቦ ያስገኘ፣ በመለኮታዊ  ሥልጣኑ የሚታየውንና የማይታየውን፣ ግዙፉንና ረቂቁን ፍጥረት ሁሉ የፈጠረ እግዚአብሔር ነው።

እግዚአብሔር ዓለምን /ፍጥረቱን/ ለመፍጠር ምክንያት የሆነው መለኮታዊ ሥልጣኑ ብቻ ነው፤ የፍጥረታት ሁሉ አስገኝ እግዚአብሔር በመሆኑም የፍጥረታት ሁሉ ጌታና ባለቤት እግዚአብሔር ነው። እግዚአብሔር ዓለምን ፈጥሮ እንዲሁ አልተወውም፤ በመግቦቱ ይጠብቀዋል፤ ይህን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ እግዚአብሔር ብቻ በመሆኑና በመለኮታዊ ሥልጣኑ መሳይ ተወዳዳሪ ስለሌለውም እግዚአብሔር አንድ አምላክ ይባላል።
 
  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

ወልድ ዋሕድ /ክፍል ፩/

 ሊቀ ካህናት ኃይለሥላሴ ዓለማየሁ ደስታ /B.D./
በዴንቨር ኮሎራዶ፣ የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም

ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪና

የሰሜን ምዕራብ አሜሪካ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ


መግቢያ፦

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንና የሌሎች አኃት አብያተ ክርስቲያናት መሠረታዊ እምነት «ተዋሕዶ» ነው። ተዋሕዶን የሚተረጉም ኃይለ ቃልም ፣ «ወልድ ዋሕድ» የሚለው ነው።

ወልድ ዋሕድ ለሚለው ሥያሜ መሠረቱ «ቃል ሥጋ ኮነ» የሚለው ቃለ ወንጌል ነው። ዮሐ ፩፥፲፬። ስለሆነም፣ የዚህ ዝግጅት ዐቢይ ርእስ /ዋና ርእስ/ ወልድ ዋሕድ እንዲባል ተመርጦአል።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

በትራክት መልክ የተዘጋጀውን ለማግኘት ይህንን ይጫኑ

መስቀሉ ከየት መጣ?

ስለ መስቀል ስንናጋር ነገርን ከሥሩ ውኃን ከጥሩ እንዲሉ ከመሠረቱ ብንናገር ይቀለናል። መስቀል በገነት ውስጥ ካሉ የተለያዩ ዕፅዋት ግኝት ነው። ከዕፅ ዘይት፣ ከዕፅ ከርካህ፣ ከዕፅ ወይራ፣ ከዕፅ ሥርናይ /ምንጭ፦ ሕማማተ መስቀል ገጽ ፴/።


ቃኤል ወንድሙ አቤልን በቅንዓት ከገደለው በኋላ ጽኑዕ የእግዚአብሔር መርገም በላዩ ላይ ወደቀበት። ደም ያሰከረው ቃኤል በምድር ላይ ኮብላይና ተቅበዝባዥ ሆነ። እርሱም ሰውን ባየ ቁጥር ይሸሻል። ሰውም በእርግማን የቆሰለው ሕይወቱን እያየ ይሸሸዋል።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
 
መስቀል

English Tract -- The Feast of the Holy Cross

ከጌታችንና ከአምላካችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ በፊት መስቀል የመቅጫ መሣሪያ ነበር። ሰውን በመስቀል ላይ መቅጣት የተጀመረውም በፋርስ ነው። ፋርስ የዛሬዋ ኢራን ናት። የፋርስ ሰዎች “ኦርሙዝድ” የተባለ “የመሬት አምላክ” ያመልኩ ነበር። ከዚህም የተነሣ “ወንጀለኛው ቅጣቱን በመሬት ላይ የተቀበለ እንደሆነ አምላካችን ይረክሳል፤” ብለው ስለሚያምኑ ወንጀለኛውን ከመሬት ከፍ አድርገው በመስቀል ላይ ይቀጡት ነበር። ይህም ቅጣት ቀስ በቀስ በሮማ ግዛት ሁሉ የተለመደ ሕግ ሆነ። ከዚህም ሌላ በኦሪቱ ሥርዓት ቅጣታቸውን በመስቀል ላይ የሚቀበሉ ሰዎች ርጉማንና ውጉዛን ነበሩ። ይህንንም እግዚአብሔር ለሙሴ “ማንም ሰው ለሞት የሚያበቃውን ኃጢአት ቢሠራ እንዲሞትም ቢፈረድበት፥ በእንጨትም ላይ ብትሰቅለው፥ በእንጨት ላይ የተሰቀለ በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና ሬሳው በእንጨት ላይ አይደር፤” ሲል ነግሮታል። /ዘዳ. ፳፩፥፳፪-፳፫/። እዚህ ላይ “በመስቀል ላይ ተሰቅሎ የሚሞት የተረገመ ከሆነ፥ ለምን ጌታችን በመስቀል ተሰቅሎ ሞተ?” እንል ይሆናል። ይህንንም እንደሚከተለው እናያለን።
  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 3 of 7First   Previous   1  2  [3]  4  5  6  7  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement