View in English alphabet 
 | Friday, March 29, 2024 ..:: ትምህርተ ሃይማኖት ::.. Register  Login
ትምህርተ ሃይማኖት

በትራክት መልክ የተዘጋጀውን መልእክት ለማግኘት እዚህ ይጫኑ

በዲ/ን ዶ/ር ንዋይ ገሠሠ

በዓለ ጰራቅሊጦስ ወይም በዓለ ጰንጠቆስጤ ከዘጠኙ የጌታችን ዐበይት በአላት አንዱ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደበትን ቀን የምናስብበት በዓል ነው። ጰራቅሊጦስ የግሪክ ቃል የሆነ የመንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ነው። ትርጉሙም በጐን የሚቆም፣ የሚረዳ፣ የሚያጽናና ማለት ነው። አበው መንጽሂ /የሚያነጻ፣ የሚቀድስ/ መጽንሂ /የሚያጸና፣ የሚያበረታ/ በማለት ይገልጹታል። ጰንጠቆስጤ የሚለውም የግሪክ ቃል ሲሆን “ፔንዲኮንዳ” ሃምሳ “ፔንዲኮስቲ” ሃምሳኛ ማለት ነው። በዓሉ ጌታችን ባረገ በአሥረኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በሃምሳኛው ቀን ይከበራል።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

ንስሐ የግዕዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙ ጸጸት ነው፡፡ ጸጸትነቱ ሰው በሠራው ኃጢአት ተጸጽቶ ኃጢአቱ ይሰረይለት ዘንድ እግዚአብሔርን በሐዘን በለቅሶ ሲለምን እንጂ የጐልማሳ ሚስት ሳልቀማ፣ የሰው ገንዘብ ሳልሰርቅ ቀረሁ … በማለት የሚጸጸተው ጸጸት አይደለም፡፡


ንስሐ ለተጠመቁ ሰዎች ከጥምቀት በኋላ የተሰጠች ሀብት ናት። በጥምቀት ከእግዚአብሔር የምትገኝ የልጅነት ሁለተኛ ማዕረግ ናት፡፡ በሃይማኖት ገንዘብ ያደረግነው የመንግሥተ ሰማያት አራቦን ማለትም መግዣ ናት። ንስሐ ለሚሿት ሰዎች የተከፈተች የይቅርታ በር ናት፡፡ በንስሐ በርነት ከፈጣሪ ወደሚገኝ ቸርነት እንቀርባለን።

ምሥጢረ ንስሐ ማለት አንድ ሰው ከጥምቀት በኋላ የፈጸመውን ጥፋት አውቆ ሁለተኛ ጥፋቱን ላለመድገም ወስኖ በእግዚአብሔርና በካህኑ ፊት ተንበርክኮ ከልቡ ተጸጽቶ ኃጢአቱን በመናዘዝ ከኃጢአቱ እስራት የሚፈታበትና ከእግዚአብሔር ይቅርታን የሚያገኝበት ታላቅ የይቅርታ ምሥጢር ነው።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

ቤተ ክርስቲያን አንዲት ናት፤ ምክንያቱም የአንድ የክርስቶስ አካል ናትና። ይህች የክርስቶስ አካል የሆነች ቤተ ክርስርስቲያን መሠረቷም ጉልላቷም ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይህንንም ታላቁ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ፦ «እርሱም (ክርስቶስ)ከሁሉ በፊት ነው፤ (ለዘመኑ ጥንት የሌለው ቀዳማዊ ነው)፤. . . እርሱም የአካሉ ማለትም የቤተ ክርስቲያን ራስ ነው፤. . . እርስዋም አካሉና ሁሉን በሁሉ የሚሞላ የእርሱ ሙላቱ ናት፤» ሲል ገልጦአታል። ኤፌ ፩፥፳፫፣ ቈላ ፩፥፲፰። በተጨማሪም በቆሮንቶስ መልእክቱ ላይ «የእግዚአብሔር ጸጋ እንደተሰጠኝ መጠን እንደ ብልሃተኛ የአናጺ አለቃ መሠረትን መሠረትሁ፥ ሌላውም በላዩ ያንጻል። እያንዳንዱ ግን በእርሱ ላይ እንዴት እንዲያንጽ ይጠንቀቅ። ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ ሊመሠርት አይችልምና፤ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።» ብሎአል። ፩ኛ ቆሮ ፫፥፲-፲፩።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

በዲ/ን ዶ/ር ንዋይ ገሠሠ
(ትራክቱን ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ)
 
 
በዓለ ጰራቅሊጦስ ወይም በዓለ ጰንጠቆስጤ ከዘጠኙ የጌታችን ዐበይት በአላት አንዱ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደበትን ቀን የምናስብበት በዓል ነው። ጰራቅሊጦስ የግሪክ ቃል የሆነ የመንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ነው። ትርጉሙም በጐን የሚቆም፣ የሚረዳ፣ የሚያጽናና ማለት ነው። አበው መንጽሂ /የሚያነጻ፣ የሚቀድስ/ መጽንሂ /የሚያጸና፣ የሚያበረታ/ በማለት ይገልጹታል። ጰንጠቆስጤ የሚለውም የግሪክ ቃል ሲሆን “ፔንዲኮንዳ” ሃምሳ “ፔንዲኮስቲ” ሃምሳኛ ማለት ነው። በዓሉ ጌታችን ባረገ በአሥረኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በሃምሳኛው ቀን ይከበራል።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

(ሊቀ ካህናት ኃይለ ሥላሴ አለማየሁ)

የጌታችን እና የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክነት ለማወቅ  የአምላክነትን የመለኮትንና የባህሪይን ትርጉምና ምሥጢር በትክክል መረዳት ያስፈልጋል:: ከዚህም ጋር አምላክ  ሰው የሆነበትን ምሥጢርና ምክንያት በሚገባ መረዳት ተገቢ ነው:: አምላክ ማለት ፈጣሪ ገዥ  ፈራጅ መጋቢ ሠራዒ ከሃሊ ማለት ነው:: አምላክነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነም እግዚአብሔር ብቻ  በመሆኑ  እሱ ብቻ የባሕርይ አምላክ ይባላል::  ፈጣሬ ዓለማት አምጻኤ ዓለማት መጋቤ ዓለማት እሱ ብቻ ነው::  ከእግዚአብሔር በቀር አምላክነት የባሕርዩ የሆነ ማንም የለም:: ኢሳ ፵፭፥፳፩- ፳፪  ፩ኛ ቆሮ ፰፥፬-፮
ሌሎች የባሕርያቸው ባልሆነ ስያሜ አማልክት እየተባሉ ቢጠሩም “አማልክት ዘበጸጋ” የጸጋ አማልክት እየተባሉ ይጠራሉ:: አማልክት ዘበጸጋ ያልሆኑትም “አማልክት ሐሰት” ሐሰተኛ አማልክት ይባላሉ እንጂ ባሕርያዊ ከሃሊነትና መለኮታዊ ሥልጣን ፈጽሞ የላቸውም ::

ዘጸ ፯፥፩ :: ዘሌ ፲፱፥፬ :: መዝ ፵፱፥፩ , ፹፩፥፩-፯ :: ኢሳ ፵፥፲፰-፲፱  ሐዋ ፲፯፥፯-፳፱

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 4 of 7First   Previous   1  2  3  [4]  5  6  7  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement