View in English alphabet 
 | Friday, April 19, 2024 ..:: ትምህርተ ሃይማኖት ::.. Register  Login
ትምህርተ ሃይማኖት

የጾም ወቅት መንፈሳዊ ተጋድሎዎች የሚበዙበት፣ ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር የምንገልጥበት፣ እምነታችን የሚጠነክርበት፣ ከዲያብሎስ ጋራ የምንዋጋበት፣ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ቅርበትና ቤተሰባዊነት የምናሻሽልበት፣ ምሥጢራችንን ለአምላካችን የምንናገርበት፣ ድሆችን የምናስብበት ጊዜ ነው፡፡ ስለዚህም የሚጾም ሁሉ በሥጋ ፈቃዱ ላይ ድል ይቀዳጃል፣ የለመነውን ያገኛል፣ ሰማያዊ የሆነውን ምሥጢር ለማየት ከዓላማዊ ነገሮች ተለይቶ ይነጠቃል፣ በዓለም እየኖረ ከዓለሙ ይለያል፡፡ ዮሐ.15÷19፡፡
  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

አዳም አባታችን ጸጋው ተገፏል፤ /ራቁትን ሆኗል፤ ኃይሉን አጥቷል፤ እንግዳ ሆኗል ባሕይርው ጐስቁሏል ሰላሙን አጥቷል፤ ነጻነቱን አጥቷል፤ ሕያውነትን አጥቷል፤ እግዚአብሔርን መምሰል አጥቷል፤ ባለዕዳ ሆኗል፤ ገነትን አጥቷል/ታዲያ አዳምን ከዚህ ሁለ ዕዳ አውጥቶ ሞትን አሸንፎ በሐዲስ ተፈጥሮ ሊፈጥረው የሚችል፤ ወደ ወጣበት ርስት የሚመልሰው ባለጸጋ የሚያደርገው ማነው?

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

የዕፀበለስ መኖር ነውን?

ዕፀ በለስ በራስዋ ማድረግ የምትችል ፍጥረት አይደለችም፡፡ ወደ አዳም ተጉዛ ብላኝ አላለችም፡፡ ደግሞም ዕፀ በለስ በአዳም ላይ ሞት ያመጣችው መርዛማ በመሆንዋ አይደለም፡፡ ዕፀ በለስ ከላይ እንዳየነው የምልክት ዛፍ ናት፡፡ ...

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

እግዚአብሔር አምላክ አምስት ቀን ሙሉ ዓለምን በሥነ ፍጥረት እያስጌጠ ካዘጋጀ በኋላ በ6ኛው ቀን ታላቁን የሥነ ፍጥረት እንግዳ ሰውን ፈጠረ፡፡ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት ስለዚህ ጉዳይ ሲያስረዱ «አንድ ደግ ሰው እንግዳ ሲጋብዝ አስቀድሞ ቤቱን፤ መብል መጠጡን ሌላውንም ነገር እንዲያዘጋጅ እግዚአሔር አስቀድሞ የሚተነፍሰውን አየር፤ የሚጠጣውን ውኃ፤ የሚበላውን ምግብ፤ የሚኖርባትን ገነት እንዲሁም ለአንክሮ ለተዘክሮ የሆኑትን ሁሉ ካዘጋጀ በኋላ አዳምን ፈጠረው፡፡»

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

መቅድም 

የመዳን ትምህርት የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ማዕከል ነው፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስም ሆነ የሌሎች መጻሕፍት ዋና ዓላማ ሰው የሚድንበትን መንገድ ማሳየት ነው፡፡ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስም የሞተው የሰወን ልጅ ለማዳን ነው፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 6 of 7First   Previous   1  2  3  4  5  [6]  7  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement