View in English alphabet 
 | Friday, March 29, 2024 ..:: ኅብረ ነገር ::.. Register  Login
ኅብረ ነገር

ወገብረ ሰላመ በዲበ መስቀሉ
በመስቀሉ ሰላምን አደረገ
 በቀሲስ ስንታየሁ ደምሴ

     መስቀል የሚለው ቃል የተገኘው “ሰቀለ” ከሚለው የግእዝ ቋንቋ ግሥ ነው፡፡ትርጓሜውም “የተመሳቀለ” ወይም “መስቀል” ማለት ነው፡፡

መስቀል ለክርስቲያኖች የሕይወትና የድኅነት ምልክት የሆነው መድኅን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ከተሰቀለበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡
 
 በኦሪት መስቀል የመርገምና የመቀጫ መሣሪያ ሆኖ ይቆጠር ነበር፡፡ ”ማንም ሰው ለሞት የሚያበቃውን ኃጢአት ቢሠራ እንዲሞትም ቢፈረድበት በእንጨትም ላይ ብትሰቅለው በእንጨት ላይ የተሰቀለ በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና ሬሳው በእንጨት ላይ አይደር” ዘዳ 21:22-23
 የጥንት ሮማውያን ወንጀለኞችን በመስቀል ተሰቅለው እንዲሞቱ ማድረግ ልማዳቸው ነበር፡፡ክርስቶስ ኢየሱስ ለድኅነተ ዓለም ከመሰቀሉ በፊት የእርግማን ምልክት የነበረው የመስቀል ታሪክ ጌታችን ከተሰቀለበት በኃላ ግን ታሪኩ ተቀይሯል፡፡PDF
  ተጨማሪ ያንብቡ


ኅብረ ነገር

ብፁዕ አቡነ አብርሃም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን አሜሪካ የሰሜን ምሥራቅና ምዕራብ አሜሪካ የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን


ኅብረ ነገር

በዐቢይ ጾም ውስጥ ካሉት ሳምንታት መካከል አራተኛው እሑድ መጻጉዕ ይባላል፡፡ መጻጉዕ የተባለበት ምክንያት በዚሁ ሰንበት ከዋዜማው ጀምሮ  የሚዘመረው ጾመ ድጓ  ድውያንን መፈወሱን ዕራንን ማብራቱን የሚያነሣ በመሆኑ ነው፡፡  «38 ዓመት የታመመውን መጻጉዕን ኢየሱስ አዳነው»  እንዲሁም ልጁ የታመመበት የመቶ አለቃው «ጌታዬ በቃልህ እዘዝ ልጄ ይድናል፡፡ በቤቴ ጣርያ ሥር አንተ ልትገባ አይገባህም» አለው:: «ጌታ በሚያልፍበት መንገድ አንድ ዕውር ፈውሰኝ» ብሎ ጮኸ የሚመሩት ሰዎች ዝም በል አሉት፡፡ ዕውሩ ግን እምቢ ብሎ «የዳዊት ልጅ ጌታ ይቅር በለኝ ዕርዳኝ» እያለ ጩኸቱን ቀጠለ፡፡
  ተጨማሪ ያንብቡ


ኅብረ ነገር

ከዐቢይ ጾም ሳምንታት ሦስተኛው ሰንበት ምኩራብ ተብሎ የተሰየመበት ምክንያት በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት «ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ»
«ኢየሱስ በሰንበት ቀን ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ» እያለ ኢየሱስ በአይሁድ ምኩራብ ማስተማሩን እየጠቃቀሰና እያነሣሣ ስለሚዘምር ይህን ሰንበት ለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ ነጋዴዎችን ለማስወጣቱ ቤተ መቅደሱን ለማስከበሩ መታሰቢያ ሆኖ ስለተሰጠ ነው፡፡ የዚህም በዓል ታሪክ ዝርዝር ሁኔታው በማቴዎስ ወንጌል ምዕ 21፡12-13 ተጠቅሷል፡፡
  ተጨማሪ ያንብቡ


ኅብረ ነገር

“እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን ዐውቀናል፡፡ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል›› (1 ዮሐ 3፡16)
በዓለማችን ላይ በተለያዩ አጋጣሚዎች ታላላቅ የኪነ ጥበብ ሰዎች፣ የታወቁ ፈላስፎች ስለ ፍቅር ብዙ ብለዋል፡፡ ይሁን እንጂ የእውነተኛውን ፍቅር ምንነቱን የገለጹት፤ በተግባርም ያዋሉት በጣም ጥቂቶች ናቸው፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 4 of 7First   Previous   1  2  3  [4]  5  6  7  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement