View in English alphabet 
 | Thursday, March 28, 2024 ..:: ዜናዎች ::.. Register  Login
ዜና

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ማኅበረ ቅዱሳን በሰሜን አሜሪካ ቺካጎ ከተማ አዲስ መንፈሳዊ የቴሌቪዥን መርሐ ግብር ጀመረ
በኢቢኤስ(EBS) በመሰራጨት ላይ የሚገኘው የማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን መርሐ ግብር በሰሜን አሜሪካ በሚገኙ 5 ከተሞች በቦስተን ፣ በካምብሪጅ ፣ በሲያትል ፣ በሚኒሶታና ሴንት ፖል ይተላለፍ የነበረውን ስርጭት በማሳደግ ስድስተኛውን ስርጭት በሰሜን አሜሪካ በመካከለኛው ምዕራብ በምትገኘው የችካጎ ከተማ ሐምሌ 25, 2007 ዓ.ም ስርጭት መጀመሩን የሰሜን አሜሪካ ማዕከል የሕትመትና ኤሌክትሮኒክስ ክፍል ገለፀ:: ስርጭቱ በችካጎና አካባቢው ለሚገኙ ምዕመናን የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማትና ለማየት በጎ ዕድል እንደሚፈጥር ሚዲያ ክፍሉ ገልጿል::

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ማኅበረ ቅዱሳን በአሜርካ ማዕከል በዳላስ ንዑስ ማዕከል ለስምንት ሳምንታት ከሰኔ 6 2007 ዓም እስከ ሐምሌ 25 2007 ዓም ሲሰጥ የነበረውን የአቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ሁለገብ ማዕከል የበጋ የሕጻናትና ታዳጊ ወጣቶች ትምህርት አጠናቆ ነሃሴ 2 2007 ዓም 50 ሕጻናት ተማሪዎችን አስመረቀ።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

በኢቢኤስ /EBS/ በመሠራጨት ላይ የሚገኘው የማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን መርሐ ግብር በሰሜን አሜሪካ በሚገኙ ሦስት ግዛቶች በቦስተን፤ በካምብሪጅ እና ሲያትል ይተላለፍ የነበረውን ሥርጭት በማሳደግ አራተኛውንና አምስተኛውን ሥርጭት በመንትያ ከተሞች /twin cites/ በሚናፖሊስ እና ሴንት ፖል ግዛቶች የካቲት 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ሥርጭት መጀመሩን የማኅበሩ የኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ዋና ክፍል ሓላፊ ዲያቆን ዶክተር መርሻ አለኸኝ ገለጹ፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

(ማኅበረ ቅዱሳን፤ ሲያትል)፦ በዋሺንግተን ዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት የሚገኙ አስራ አራት (14) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት በአንድነት በመሆን የ2007 ዓ.ም የከተራና የጥምቀት በዓልን በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል።

 

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙ 13 አብያተ ክርስቲያናት አንድ ላይ በመሆን የመስቀል ደመራ በዓልን ዓርብ መስከረም 16 ቀን 2007 ቨርጂኒያ ግዛት አሌክሳንደርያ ከተማ በሚገኘው በቤን ብረንማን ፓርክ ከቀኑ 4 ጀምሮ የዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል።

በዋሽንግተን ግዛት፣ በሲያትልና አካባቢ የሚገኙ አምስት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በመተባበር ከየአጥቢያው በመጡ አበው ካህናት፣ ዲያቆናት፣ የሰንበት ት/ቤት አባላት እንዲሁም ምእመናንና ምእመናት በተገኑበት መስከረም 18 በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።

 

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 1 of 13First   Previous   [1]  2  3  4  5  6  7  8  9  10  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement