እንደ ዲያቆን ዶክተር መርሻ ገለጻ ዋና ክፍሉ ለአሜሪካ ማእከል በሰጠው አቅጣጫ መሠረት ከቤተ ክርስቲያን መዋቅር ጋር በመቀናጀት ሥርጭቱ በሁሉም ግዛቶች እንዲያድግና ተግባራዊ እንዲሆን የማእከሉ አባላት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው፤ ዝግጅቶቹን ለማሰራጨት የግዛቶቹ ባለሥልጣናት ስቱዲዮ በመስጠት ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በኢቢኤስ የሚተላለፈው የማኅበሩ የቴሌቪዥን ሥርጭት ከአንድ ሰዓት በላይ ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ሲሆን፤ ከዚህ በተጨማሪም የኢንተርኔት ቴሌቪዥን መርሐ ግብር ለመጀመር ዝግጅቱ እየተጠናቀቀ እንደሚገኙም ዲያቆን ዶክተር መርሻ ገልጸዋል::