View in English alphabet 
 | Friday, April 19, 2024 ..:: ዜናዎች ::.. Register  Login
ዜና

የከምባታ፣ ሐድያ፣ ጉራጌና ስልጢ አህጉረ ስብከተ ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የነበሩት ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ዐረፉ፡፡
ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ በደረሰባቸው ሕመም ሳቢያ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ሰኔ 13 ቀን 2002 ዓ.ም ዐርፈዋል፡፡

ሥርዓተ ቀብራቸው ሰኔ 15 ቀን 2002 ዓ.ም ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ካህናት አባቶችና ምእመናን በተገኙበት በምሁር ኢየሱስ ገዳም ተፈጽሟል፡፡ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ያስተዳድሩት በነበረው ሀገረ ስብከት ውስጥ በሚገኘው እዣና ወለኔ ወረዳ /ምሁር ኢየሱስ ገዳም አካባቢ/ ከአባታቸው ከመምሬ ክንፈ ሚካኤልና ከእናታቸው ከወ/ሮ አስካለ ማርያም በ1951 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት እንደደረሰ የምሁር ኢየሱስ ገዳም ቄሰ ገበዝ የነበሩት አባታችው በዚያው ፊደልና የቁጥር ትምህርት አስተማሯቸው፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

በጣና ሐይቅ ዙሪያ ከሚገኙት የዘጌ ገዳማት መካከል አንዱ የሆነው የመሐል ዘጌ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን  የካቲት 5 ቀን 2002 ዓ.ም ከቀኑ  12፡00 ሰዓት ጀምሮ የአደጋዉ ምክንያት ባልታወቀ እሳት ሙሉ በሙሉ ወድሟል። እሳቱን  ለማጥፋት በገዳሙ ዙሪያ የሚገኙ ምዕመናን፣ በአካባቢው የሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል እና ከባሕር ዳር ከተማ በጀልባ ተሳፍረው የሄዱ ምዕመናን ጥረት ቢያደርጉም የእሳቱን ቃጠሎ ለመከላከል እና ለማጥፋት ሳይቻላቸው ቀርቷል።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

(በሻምበል ጥላሁን):
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የነገረ መለኮት ምሩቃን ማኅበር ከአሶሳ ሀገረ ስብከት ጋር በመተባበር ባደረገው ሐዋርያዊ ጉዞ ከአራት ሺሕ በላይ ሰዎች የክርስትና ጥምቀት እንዲጠመቁ ማስቻሉን አስታወቀ፡፡ "የነገረ መለኮት ምሩቃን ማኅበር" ለስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል በላከው መረጃ እንዳስታወቀው፤ ሐዋርያዊ ጉዞና ጥምቀቱ የተከናወነው ከታኅሣሥ 16 እስከ 25 ቀን 2002 ዓ. ም የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ፣ ሥራ አስኪያጁ ሊቀ መዘምራን ሐረገወይን ጫኔ፣ የከማሽ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ መልአከሰላም ተገኝ ጋሻው በተገኙበት ነው፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

(በደረጀ ትዕዛዙ)

በማኅበረ ቅዱሳን የሕንፃ ግንባታ ጽ/ቤት አሳታሚነት ለኅትመት የበቃው «እመ ምኔት» የተሰኘው የደራሲ ፀሐይ መላኩ አዲስ ረጅም ልብወለድ መጽሐፍ ተመረቀ፡፡  ጥር 9 ቀን 2002 ዓ.ም አንጋፋና ወጣት ደራሲያን፣ የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በሩስያ ባህል ማዕከል /ፑሽኪን አዳራሽ/ የተመረቀው መጽሐፍ፤ በገዳማውያን ሕይወትና በውስብስብ ወንጀል ታሪክ ላይ ያተኮረ ሲሆን ደራሲዋ የመጽሐፉን ሸያጭ ገቢ ለማኅበሩ ጽ/ቤት ሕንፃ ግንባታ እንዲውል አበርክተዋል፡፡ የማኅበረ ቅዱሳን ምክትል ዋና ጸሐፊ እና የሕንፃ አሠሪ ኮሚቴው ተወካይ ዲያቆን ዋስይሁን በላይ በዚሁ ምረቃ ወቅት ባስተላለፉት መልእክት፤ ማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር ሆኖ ለበርካታ ዓመታት መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ሲያበረክት መቆየቱን ጠቅሰው ይህንኑ አገልግሎት በተጠናከረ ሁኔታ ለማከናወን የጽ/ቤት ሕንፃ ግንባታ እያካሄደ ነው ብለዋል፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኀበረ ቅዱሳን ጥር 22 እና 23 2002 ዓ.ም በሎስ አንጀለስ ያቀረበው ዐውደ ርእይ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን የዝግጅቱ አስተባባሪዎች አስታወቁ:: ቅዳሜ ጥር 22 ቀን 2002 ዓ.ም ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ከሎስ አንጀለስ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን፣ ከላስ ቬጋስ ቅዱስ ሚካኤል ወቅድስት ኪዳነ ምሕረት እንዲሁም ከፖርትላንድ በተጋበዙ ቆሞሳትና ቀሳውስት በጸሎት ከተከፈተ ጊዜ ጀምሮ ለሁለት ቀናት በቆየው በዚሁ ዐውደ ርእይ ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ እንግሊዘኛ ተናጋሪዎች እንዲሁም ኢትዮጵያውያን መመልከት እንደቻሉ ታውቋል::

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 10 of 13First   Previous   4  5  6  7  8  9  [10]  11  12  13  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement