View in English alphabet 
 | Saturday, April 27, 2024 ..:: ዜናዎች ::.. Register  Login
ዜና

`አንድ መጽሐፍ ይለግሱ´ በሚል መሪ ቃል በገጠር እና ጠረፋማ አካባቢ ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት፤ ለሰንበት ት/ቤቶችና ለአብነት ት/ቤቶች የመጽሐፍ ድጋፍ ለማሰባሰብ የሚያስችል መርሐ ግብር በማኀበረ ቅዱሳን ሊጀመር ነው፡፡

በገጠር እና ጠረፋማ አካባቢ ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ፡ ሰንበት ት/ቤቶች እንዲሁም ለአብነት ት/ቤቶች የመጽሐፍት ድጋፍ ለማሰባሰብ የተዘጋጀ ፕሮጀክት

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

 በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ በሌመን ወረዳ በሚገኘው አዳዲ ደብረ ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቤተ መቅደስ ውስጥ የፎቶ ግራፍ ባለሙያ በመምሰል ገብቶ «አላህ አክበር» ሲል የተገኘው የእስልምና እምነት ተከታይ በአንድ ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ፡፡

የሌመን ወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የቤተ ክርስቲያኗ አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ተስፋዬ አባተ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለፁት፤ ኅዳር 21 ቀን 2001 ዓ.ም ከቀኑ 4 ሰዓት ቤተ መቅደስ ውስጥ ገብቶ «አላህ አክበር» በማለት የቤተ ክርስቲያኑን ሥርዓተ ጸሎት በማወኩ በምእመናን ትብብር በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ሊውል ችሏል፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በሰ/ት/ቤ/ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን በአሜሪካ ማዕከል አዘጋጅነት በአትላንታ ጆርጂያ ኅዳር 13 እና 14 ለሁለት ቀናት ክፍት ሆኖ የቆየው ‹‹የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን፡- ትናንት - ዛሬ - ነገ›› ዐውደ ርእይ በደመቀ ሁኔታ ተጠናቀቀ፡፡ ፎቶዎችን እዚህ ይመልከቱ፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

(አዲስ አበባ)፡- ቤተ ክርስቲያን በ 2000 ዓ.ም ባከናወነቻቸው ተግባራትና ስለ አጋጠሟት ችግሮች የመከረው 27ኛው የመንበረ ­ትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ከጥቅምት 7-11 ቀን 2001 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተካሔደ፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና



Page 12 of 13First   Previous   4  5  6  7  8  9  10  11  [12]  13  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement