View in English alphabet 
 | Friday, March 29, 2024 ..:: ፕሮጀክቶች ::.. Register  Login
ፕሮጀክቶች

“ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፤ እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል።” መዝ 40፤1

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን!

ከሳዑዲ አረቢያ በአግባቡ ሳያስቡበትና ሳይዘጋጁ በድንገት ወደሀገራቸው በህይወት ተርፈው የተመለሱት ወገኖቻችን ባዶ እጃቸውን በመሆናቸው በአሁኑ ጊዜ ለዕለት ጉርስና ለአመት ልብስ የሚሆን በቂ ነገር የላቸውም። በመጽሐፍ እነደተገለጸው “እንጀራህን ለተራበ ትቆርስ ዘንድ፤ ስደተኞችን ድሆች ወደቤትህ ታገባ ዘንድ፤ የተራቆተውን ብታይ ታለብሰው ዘንድ” ብሎ እግዚአብሔር ያዛልና ኢሳ 58፤7 ለወገን ደራሽ ወገን መሆኑን የምንገልጥበት አጋጣሚ አሁን ነው።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ፕሮጀክቶች

ስትመጣ . . . መጻሕፍቱንም ይልቁንም በብራና የተጻፉትን አምጣልኝ ፪ ጢሞ ፬፡፲፫

"የአኮቴት እና የስጦታ ሰሞን"

በዋናው ማእከል ማኀበረ ቅዱሳን የቤተ መጻሕፍትና ቤተ መዛግብት ክፍሉን በዘመናዊ መልኩ ለማደራጀት እና አገልግሎቱን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ከአሜሪካውያን ታንክስ ጊቪንግ (የአኮቴት ቀን) ህዳር 16 እስከ ኢትዮጵያውያን የገና በአል ታህሳስ 29 የሚቆይ የስጦታ ማሰባሰቢያ ቀን ተዘጋጅቷል።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ፕሮጀክቶች

  


ፕሮጀክቶች

 በትራክት መልክ የተዘጋጀውን መልእክት ለማግኘት እዚህ ይጫኑ

 

“እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ ” ማቴ 28፥19-20

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !

ለተወደዳችሁ የክርስቶስ ቤተሰቦች !

ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችን  ጋር ይሁን !

ጉዳዩ : ለ10 ዓመቱ የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮጀክት ድጋፍ ስለመጠየቅ

ማኅበራችን ማኅበረ ቅዱሳን ቅዱስ ሲኖዶስ የሰጠውን ሓላፊነት ለመወጣት በተለያዩ መንገዶች ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፤ እያደረገም ይገኛል፡፡ ሆኖም ግን ሁሉንም የቤተክርስቲያን አባላት ባሳተፈ እና ሁሉም ምዕመናን የድርሻቸውን እንዲወጡ በማድረግ ችግሩን ለመቅረፍ ይቻል ዘንድ፤ ስብከተ ወንጌል አገልግሎት ባልተስፋፋባቸው ገጠርና ጠረፋማ ቦታዎች፤ አኅዛብና መናፍቃን በበዛባቸው አካባቢዎች ወንጌልን ለማዳረስ የአሥር ዓመት የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ማስፋፊያ ኘሮግራም በመቅረጽ በግንቦት 19/2002 ዓ.ም. አገልግሎቱን ጀምሯል፡፡ 

  ተጨማሪ ያንብቡ


ፕሮጀክቶች

የ2003 ዓ.ም. ሪፖርት

በ2003 ዓ.ም. ከተሠሩት ሥራዎች በፎቶግራፍ


ለ2004 ዓ.ም. የታቀዱ ሥራዎችን ያካተተ ሊፍሌት

  


Page 1 of 2First   Previous   [1]  2  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement