View in English alphabet 
 | Friday, April 26, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
አማርኛ




ላክ   ተወው
ዜና

በማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል “በእንተ ስማ ለማርያም” (ስለ እመቤታችን ማርያም ! ) በሚል መሪ ቃል ያሰናዳው በአብነት ትምህርት ቤቶች ዙሪያ ላይ ያተኮረው ብዙኃን የቤተክርስቲያን ልጆች የተሳተፉበት ዐውደ ርዕይ በሲያትል ንዑስ ማዕከል አዘጋጅነት መጋቢት 7 እና መጋቢት 8 2005 ዓ/ም በሲያትል የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አዳራሽ ለሕዝብ እይታ ቀርቧል::  

ዐውደ ርዕዩ ቅዳሜ መጋቢት 7 2005 ዓ/ም በሲያትልና በአቅራቢያው ካሉ ከተሞች በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች፣ የሰባካ ጉባኤ አባላት፣ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው  እንግዶች በተገኙበት ደመቅ ባለ ሥነ ሥርዓት ተከፍቷል::
በዚሁ ወቅት  በማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል  መልእክት በዲ/ ተገኔ ተክሉ  የቀረበ ሲሆን በመክፈቻው ላይ በተገኙ ካህናትና ተጋባዥ እንግዶች የተለያየ አስተያየት ተሰጥቷል።
ለሁለት ቀን ክፍት ሆኖ የቆየውን ዐውደ ርዕይ  ከ300 በላይ ምእመናን የተመለከቱት ሲሆን ከተሰበሰበውን አስተያየት  የብዙኃኑን ስሜት የነካ እንደነበረ ለመረዳት ተችሏል። ዓውደ ርእዩን የተመለከቱ ምእመናን በዕለቱ ቀረበው ከነበሩት ፕሮጀክቶችን  መካከል እየመረጡ የወሰዱ ሲሆን በኦንላይን በተዘጋጀው የልገሳ ድረ ገጽ (http://www.gedamat.org)  ላይ አስተዋጽኦ አድርገዋል።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ፕሮጀክቶች

  


የቤተ ክርስቲያን ታሪክ

ቤተ ክርስቲያን ሲባል የተለያዩ ትርጉሞች አሉት። በዚህም መሠረት ቤተ ክርስቲያን ሲባል  ክርስቲያን ምእመናን፣ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች፣ የቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና የቤተ ክርስቲያን ሕንጻ ሲሆን ይችላል። የእነዚህንም አባባሎች ዝርዝር ሁኔታዎች በሚቀጥሉት መግለጫዎች እንመልከት።

ምእመናን፦ በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተጠመቁና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያመኑ የክርስቲያን ሃይማኖት ምእመናን ቤተ ክርስቲያን ይባላሉ።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

“ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኀጢአት፣ ኀጢአትን በምታስተሠርይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን”
/ጸሎተ ሃይማኖት/

ጥምቀተ ክርስቶስ

ለጌታችን ሠላሳ ዓመት ሊሆነው ስድስት ወር ሲቀረው ፣ የሊቀ ካህናቱ የዘካርያስ ልጅ ዮሐንስ ከምድረ በዳ ወጥቶ ማስተማር ጀመረ:: ይህንንም ትምህርት የጀመረው ከፈጣሪው ባገኘው መልእክት ነው:: ሉቃ ፫፥፩ ዮሐንስም ከቆሮንቶስ ምድረ በዳ ወጥቶ በዮርዳኖስ ዙርያ “መንግስተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” እያለ በማስተማር የንስሐን ጥምቀት ማጥመቅ ጀመረ :: ሉቃ ፫፥፫ ሕዝቡም ትምህርቱን በመቀበል ኃጢአታቸውን እየተናዘዙ በንስሐ ጥምቀት ይጠመቁ ነበር:: ማቴ ፫፥፫ የትምህርቱን እውነተኛነት ባወቁ ጊዜ ዮሐንስን ክርስቶስ ነው ብለው ጠረጠሩ:: ሉቃ ፫፥፲፭ ዮሐንስም እንዲህ ሲል እውነቱን ነገራቸው " እርሱም፦ ነቢዩ ኢሳይያስ እንዳለ። የጌታን መንገድ አቅኑ ብሎ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ እኔ ነኝ አለ። የተላኩትም ከፈሪሳውያን ነበሩና። እንኪያስ አንተ ክርስቶስ ወይም ኤልያስ ወይም ነቢዩ ካይደለህ፥ ስለ ምን ታጠምቃለህ? ብለው ጠየቁት።  ዮሐንስ መልሶ፦ እኔ በውኃ አጠምቃለሁ፤ ዳሩ ግን እናንተ የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሞአል፤  እኔ የጫማውን ጠፍር ልፈታ የማይገባኝ፥ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ከእኔ ይልቅ የሚከብር ይህ ነው አላቸው። ይህ ነገር ዮሐንስ ያጠምቅበት በነበረው በዮርዳኖስ ማዶ በቢታንያ በቤተ ራባ ሆነ። በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ። አንድ ሰው ከእኔ በኋላ ይመጣል፥ ከእኔም በፊት ነበርና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል ብዬ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነው።" ዮሐ ፩፥፳

  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

መጋቤ ብሉይ አእምሮ ዘውዴ

እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ  አይደለም፡፡ ከጥንት ከመሠረት ጀምሮ በመላእክት፤ በነቢያት  ሲነገር፤ ሲሰበክ የመጣ ነው እንጂ፡፡ ማቴ.1፥18፡፡
ሰው የመሆኑን ምሥጢር ለመጀመሪያ ጊዜ በማእከለ ገነት የተናገረ እርሱ እግዚአብሔር ነው፡፡

አባታችን አዳም ከእግዚአብሔር ትእዛዝ ወጥቶ ዕፀ በለስን በልቶ ከጸጋ እግዚአብሔር በተራቆተ ጊዜ /አዳም ኮነ ከመ አሐዱ እምኔነ/ አዳም ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ ዘፍ.3፥22 ብሎ ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው እንደሚሆን ተናግሯል፡፡ በዚህ ቃል መሠረት /መሪነት/ ቅዱሳን መላእክት ምሥጢረ ትንቢት ተገልጾላቸዋል፡፡ እነሱም የተገለጸላቸውን ምሥጢረ ትንቢት ኀላፍያትንና መጻእያትን ለሚናገሩ ነቢያት ነግረዋቸዋል፡፡ ቅዱሳን ነቢያትም ከእግዚአብሔር ያገኙትን ከመላእክት የሰሙትን መነሻ አድርገው በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ምሳሌያት በተለያዩ ዘመናት የወልደ እግዚአብሔርን ሥጋዌ ሰብከዋል /ገልጸዋል/ ዕብ.1፥1፡፡ ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ፥ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 11 of 41First   Previous   6  7  8  9  10  [11]  12  13  14  15  Next   Last   

 የ10 ዓመት የስብከተ ወንጌል ማስፋፋፊያ ፕሮጀክት Minimize

ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት እና ለመርዳት ይህንን ይጫኑ።


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ሶሻል ኔትወርኪንግ

Share |

  
 ግጻዌ


  
 የተላለፉ የቴሌቪዥን እና ሬዲዮ መርሃ ግብር ለመከታተል Minimize


  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement