View in English alphabet 
 | Thursday, April 25, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
አማርኛ




ላክ   ተወው
ፕሮጀክቶች

 በትራክት መልክ የተዘጋጀውን መልእክት ለማግኘት እዚህ ይጫኑ

 

“እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ ” ማቴ 28፥19-20

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !

ለተወደዳችሁ የክርስቶስ ቤተሰቦች !

ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችን  ጋር ይሁን !

ጉዳዩ : ለ10 ዓመቱ የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮጀክት ድጋፍ ስለመጠየቅ

ማኅበራችን ማኅበረ ቅዱሳን ቅዱስ ሲኖዶስ የሰጠውን ሓላፊነት ለመወጣት በተለያዩ መንገዶች ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፤ እያደረገም ይገኛል፡፡ ሆኖም ግን ሁሉንም የቤተክርስቲያን አባላት ባሳተፈ እና ሁሉም ምዕመናን የድርሻቸውን እንዲወጡ በማድረግ ችግሩን ለመቅረፍ ይቻል ዘንድ፤ ስብከተ ወንጌል አገልግሎት ባልተስፋፋባቸው ገጠርና ጠረፋማ ቦታዎች፤ አኅዛብና መናፍቃን በበዛባቸው አካባቢዎች ወንጌልን ለማዳረስ የአሥር ዓመት የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ማስፋፊያ ኘሮግራም በመቅረጽ በግንቦት 19/2002 ዓ.ም. አገልግሎቱን ጀምሯል፡፡ 

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

በትራክት መልክ የተዘጋጀውን መልእክት ለማግኘት እዚህ ይጫኑ

በዲ/ን ዶ/ር ንዋይ ገሠሠ

በዓለ ጰራቅሊጦስ ወይም በዓለ ጰንጠቆስጤ ከዘጠኙ የጌታችን ዐበይት በአላት አንዱ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደበትን ቀን የምናስብበት በዓል ነው። ጰራቅሊጦስ የግሪክ ቃል የሆነ የመንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ነው። ትርጉሙም በጐን የሚቆም፣ የሚረዳ፣ የሚያጽናና ማለት ነው። አበው መንጽሂ /የሚያነጻ፣ የሚቀድስ/ መጽንሂ /የሚያጸና፣ የሚያበረታ/ በማለት ይገልጹታል። ጰንጠቆስጤ የሚለውም የግሪክ ቃል ሲሆን “ፔንዲኮንዳ” ሃምሳ “ፔንዲኮስቲ” ሃምሳኛ ማለት ነው። በዓሉ ጌታችን ባረገ በአሥረኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በሃምሳኛው ቀን ይከበራል።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

የማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል ዓመታዊ ጉባኤ ተካሔደ

• 20ኛ የምሥረታ በዓሉም ተከበረ

(ዴንቨር፣ ኮሎራዶ)፦ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከሉ በየዓመቱ የሚያካሒደው ጠቅላላ ጉባዔ የዚህ ዓመት ስብሰባ ግንቦት 18-19/2004 ዓ.ም በኮሎራዶ ግዛት የዴንቨር ከተማ ተካሔደ። በመላው አሜሪካ ከሚገኙ 11 ንዑሳን ማዕከላት (ቀጣና ማዕከላት) እና 2 ግንኙነት ጣቢያዎች የመጡ አባላት በተሰበሰቡበት በዚህ ጉባኤ ላይ ከዋናው ማዕከል የተወከሉ ሦስት ልዑካን፣ የካሊፎርኒያና የምዕራብ ስቴቶች ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት ኃ/ሥላሴ ዓለማየሁ፣ አበው ካህናት እና ተጋባዥ እንግዶች የተገኙ ሲሆን በዓመታዊ አገልግሎት ሪፖርትና ዕቅድ እንዲሁም በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሒዷል።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና



ማኅበረ ቅዱሳን

ማሩ አይምረር፤ ወተቱ አይጥቆር

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ

“ማኅበረ ቅዱሳን”

ሚያዚያ 24/2004 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር ተዋቅሮ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን በእግዚአብሔር ፈቃድ አገልግሎቱን ከጀመረ እነሆ ሃያ ዓመታት ተቆጠሩ። ምንም እንኳን ማኅበሩን በራሳቸው ፈቃደኝነት የተሰባሰቡ ኦርቶዶክሳውያን ቢመሠርቱትም የማኅበሩ መሠረታዊ ዓላማ ግን ቤተ ክርስቲያን ተልእኮዋን ለማሳካት በምታከናውናቸው ተግባራት የልጅነት ድርሻውን ለመወጣት በመሆኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን መዋቅር በመግባት መተዳደሪያ ደንቡ በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በተቀመጠለት ተግባርና ሓላፊነት መሠረት አገልግሎቱን እያከናወነ ያለ ማኅበር ነው። አባላቱም በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ ሀገራት በቤተ ክርስቲያኗ አጥቢያዎች በሚገኙ ሰበካ ጉባኤያት እና ሰንበት ት/ቤቶች ተመዝግበው የሚጠበቅባቸውን ክርስቲያናዊ ግዴታ እየተወጡ ይገኛሉ። እነዚህ አባላት አብዛኛዎቹ ቤተ ክርስቲያናቸውን በገንዘብ፣ በዕውቀትና በጉልበት ለማገልገል በፈቃዳቸው ቃል የገቡ ቤተ ክርስቲያንና ሀገሪቷ ካሏት ልዩ ልዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመርቀው ቤተ ክርስቲያናቸውን አገራቸውንና ወገናቸውን በልዩ ልዩ ሙያ እያገለገሉ የሚገኙ ናቸው።
ተጨማሪ ያንብቡ
  


Page 16 of 41First   Previous   11  12  13  14  15  [16]  17  18  19  20  Next   Last   

 የ10 ዓመት የስብከተ ወንጌል ማስፋፋፊያ ፕሮጀክት Minimize

ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት እና ለመርዳት ይህንን ይጫኑ።


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ሶሻል ኔትወርኪንግ

Share |

  
 ግጻዌ


  
 የተላለፉ የቴሌቪዥን እና ሬዲዮ መርሃ ግብር ለመከታተል Minimize


  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement