View in English alphabet 
 | Saturday, April 20, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
አማርኛ




ላክ   ተወው
ትምህርተ ሃይማኖት

(ሊቀ ካህናት ኃይለ ሥላሴ አለማየሁ)

የጌታችን እና የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክነት ለማወቅ  የአምላክነትን የመለኮትንና የባህሪይን ትርጉምና ምሥጢር በትክክል መረዳት ያስፈልጋል:: ከዚህም ጋር አምላክ  ሰው የሆነበትን ምሥጢርና ምክንያት በሚገባ መረዳት ተገቢ ነው:: አምላክ ማለት ፈጣሪ ገዥ  ፈራጅ መጋቢ ሠራዒ ከሃሊ ማለት ነው:: አምላክነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነም እግዚአብሔር ብቻ  በመሆኑ  እሱ ብቻ የባሕርይ አምላክ ይባላል::  ፈጣሬ ዓለማት አምጻኤ ዓለማት መጋቤ ዓለማት እሱ ብቻ ነው::  ከእግዚአብሔር በቀር አምላክነት የባሕርዩ የሆነ ማንም የለም:: ኢሳ ፵፭፥፳፩- ፳፪  ፩ኛ ቆሮ ፰፥፬-፮
ሌሎች የባሕርያቸው ባልሆነ ስያሜ አማልክት እየተባሉ ቢጠሩም “አማልክት ዘበጸጋ” የጸጋ አማልክት እየተባሉ ይጠራሉ:: አማልክት ዘበጸጋ ያልሆኑትም “አማልክት ሐሰት” ሐሰተኛ አማልክት ይባላሉ እንጂ ባሕርያዊ ከሃሊነትና መለኮታዊ ሥልጣን ፈጽሞ የላቸውም ::

ዘጸ ፯፥፩ :: ዘሌ ፲፱፥፬ :: መዝ ፵፱፥፩ , ፹፩፥፩-፯ :: ኢሳ ፵፥፲፰-፲፱  ሐዋ ፲፯፥፯-፳፱

  ተጨማሪ ያንብቡ


ኅብረ ነገር

  


ፕሮጀክቶች



ነገረ ቅዱሳን

የሰው ልጆች ወደ እግዚአብሔር በመንፈሳዊ አገልግሎት ባዘነበሉ መጠን ቸርነት የባሕርዩ የሆነ እግዚአብሔር ደግሞ የተለያየ መንፈሳዊ ብቃትን ይሰጣቸዋል፤ ሰማያዊ ምሥጢርን ይገልጥላቸዋል። ቅዱሳን በሥጋቸው በምድር ለጸሎት ቆመው ነፍሳቸው በተመስጦ ገነት መንግሥተ ሰማያት ተነጥቃ ሄዳ ከቅዱሳን መላእክት ጋር ታመሰግናለች። እንዲሁም በአካል እንደ ነቢያቱ ሄኖክና ኤልያስ በመወሰድ እስከ ጌታችን ዳግም ምጽአት መዳረሻ ቀን በመሰወር እንደሚኖሩ ቅዱሳት መጻሕፍት ያስረዱናል።

«መሰወር» የሚለው ቃል የግእዝ ግሱ «ኀብአ»፦ «ሰወረ፥ መሰወር»፤ «ተኀብአ»፦ «ተደበቀ፥ ተሰወረ፥ ራቀ፥ ረቀቀ» ማለት ሲሆን በጥቅሉ ለዓይን እንዳይታይ እንዳይገኝ ሆነ፤ ለምሥጢርም ከሆነ ለአእምሮ ረቀቀ ማለት ነው ።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

በዲ/ን አሉላ መብራቱ
 
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት (ዘወረደ) ለአጠቃላይ ጾሙ መግቢያ የሚሆኑ ሦስት መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ትምህርቶች(መልዕክቶች) ይተላለፉበታል። እነዚህን ቀጥለን እንመለከታለን።
 
1.    ስለጾም
 
ዘወረደ የታላቁ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ስለሆነ ቤተ ክርስቲያን የጾም አዋጅ ታውጅበታለች፤ ስለ ጾም ጥቅምና እንዴት መጾም እንዳለብን ታስተምረናለች፡፡ጾመ ድጓው “አከለክሙ መዋእል ዘኃለፈ ዘተቀነይክሙ ለግእዘ ሥጋክሙ፤ ለሥጋቸሁ ፈቃድ የተገዛችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃችኋል፤ ከአሁን በኋላ ግን ጹሙ፣ ጸልዩ ለእግዚአብሔር ተገዙ” እያለ የጾም አዋጅ ያውጃል።
  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 28 of 41First   Previous   23  24  25  26  27  [28]  29  30  31  32  Next   Last   

 የ10 ዓመት የስብከተ ወንጌል ማስፋፋፊያ ፕሮጀክት Minimize

ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት እና ለመርዳት ይህንን ይጫኑ።


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ሶሻል ኔትወርኪንግ

Share |

  
 ግጻዌ


  
 የተላለፉ የቴሌቪዥን እና ሬዲዮ መርሃ ግብር ለመከታተል Minimize


  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement