View in English alphabet 
 | Tuesday, April 23, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
አማርኛ




ላክ   ተወው
ትምህርተ ሃይማኖት

(በመሐር ቸሬ አበበ)
በፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊ አንቀጽ 15 እንደተገለጸው ቅዱሳን አባቶቻችን ሥጋ ለነባቢት ነፍስ እንድትታዘዝና የፈቲው ፆርም እንዲደክም የሚያደርግ የሰውን ልጅ ከእግዚአብሔር ጋር እንዲገናኝ የለመነውም ልመና መልስ እንዲኖረው እጅግም የሰይጣንን ፍላጻ ወይም ጦር ለመስበር የሚያስችል ኃይል ያለው መሣሪያ ጾም ነው፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር «በእግዚአብሔር አምላካችን ፊት ራሳችንን ዝቅ እናድርግ፣ በእርሱም ዘንድ ጾምን አወጅኩኝ። ስለዚህ ነገር ጾምን፣ ወደ እግዚአብሔርም ለመንን እርሱም ተለመነን፡፡» እንዳለ የሰው ልጅ የነፍሱን ነገር በማሰብ በጾም እግዚአብሔርን ሊለምን ሊማጸን የሚፈልገውን ሁሉ ሊጠይቅ ይገባል፡፡ ከነቢዩ ዕዝራ የምንማረው በጾም ለሕዝብና ለራስ ለምኖ ዋጋ ማግኘትን ነው፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

(በቀሲስ ስንታየሁ አባተ)
በኢሳይያስ ዘመን የነበሩ እስራኤላውያን የተናገሩት ቃል ነው:: እስራኤላውያን የሚጾሟቸው ብዙ አጽዋማት ነበሯቸው:: ለምሳሌ ያህልም ብናይ በሳምንት ሁለት ጊዜ በሳምንት ሁለት ቀን ይጾሙ እንደነበር በሉቃስ ወንጌል ምዕ. 18¸12 ላይ ያለው ቃል ያስረዳል:: ማክሰኞና ሐሙስ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ወደ ደብረ ሲና የወጣበትንና ከዚያ የወረደበትን ዕለት ለማሰብ እስራኤላውያን በሳምንት ሁለት ቀኖች ይጾሙ ነበR:: በነቢዩ በዘካርያስ ትንቢትም ላይ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን እንዲህ ብሎ አዝዟቸዋል::"የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል የአራተኛው ወር ጾም የአምስተኛውም የሰባተኛውም የአስረኛውም ወር ጾም ለይሁዳ ቤት ደስታና ተድላ የሀሴትም በዓላት ይሆናል ስለዚህም እውነትንና ሰላምን ወደዱ" ተብሎ ለእስራኤላውያን ከእግዚአብሔር ዘንድ በነቢዩ በኩል በተነገራቸው መሠረት የተጠቀሱትን ይጾሙ ነበረ:: ዘካ. 8 18ና19

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ባሕልና ትውፊት መሠረት ይህ የያዝነው የጾም ወራት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱና ዋነኛው፣ ጌታ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው የአርባ ቀን ጾም ነው፡፡ ምእመናን ጌታቸው ያደረገውን ምሳሌ ተከትለው ይጾሙታል፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

የጾም ወቅት መንፈሳዊ ተጋድሎዎች የሚበዙበት፣ ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር የምንገልጥበት፣ እምነታችን የሚጠነክርበት፣ ከዲያብሎስ ጋራ የምንዋጋበት፣ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ቅርበትና ቤተሰባዊነት የምናሻሽልበት፣ ምሥጢራችንን ለአምላካችን የምንናገርበት፣ ድሆችን የምናስብበት ጊዜ ነው፡፡ ስለዚህም የሚጾም ሁሉ በሥጋ ፈቃዱ ላይ ድል ይቀዳጃል፣ የለመነውን ያገኛል፣ ሰማያዊ የሆነውን ምሥጢር ለማየት ከዓላማዊ ነገሮች ተለይቶ ይነጠቃል፣ በዓለም እየኖረ ከዓለሙ ይለያል፡፡ ዮሐ.15÷19፡፡
  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኀበረ ቅዱሳን ጥር 22 እና 23 2002 ዓ.ም በሎስ አንጀለስ ያቀረበው ዐውደ ርእይ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን የዝግጅቱ አስተባባሪዎች አስታወቁ:: ቅዳሜ ጥር 22 ቀን 2002 ዓ.ም ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ከሎስ አንጀለስ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን፣ ከላስ ቬጋስ ቅዱስ ሚካኤል ወቅድስት ኪዳነ ምሕረት እንዲሁም ከፖርትላንድ በተጋበዙ ቆሞሳትና ቀሳውስት በጸሎት ከተከፈተ ጊዜ ጀምሮ ለሁለት ቀናት በቆየው በዚሁ ዐውደ ርእይ ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ እንግሊዘኛ ተናጋሪዎች እንዲሁም ኢትዮጵያውያን መመልከት እንደቻሉ ታውቋል::

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 33 of 41First   Previous   28  29  30  31  32  [33]  34  35  36  37  Next   Last   

 የ10 ዓመት የስብከተ ወንጌል ማስፋፋፊያ ፕሮጀክት Minimize

ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት እና ለመርዳት ይህንን ይጫኑ።


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ሶሻል ኔትወርኪንግ

Share |

  
 ግጻዌ


  
 የተላለፉ የቴሌቪዥን እና ሬዲዮ መርሃ ግብር ለመከታተል Minimize


  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement