View in English alphabet 
 | Thursday, April 25, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
አማርኛ




ላክ   ተወው
ነገረ ቅዱሳን

የቅድስት አርሴማ ወላጆች አባቷ ቴዎድሮስ እናቷ አትናትያስ ይባላሉ:: በፈሪሃ እግዚአብሔር  በአምልኮ ጸንተው በሕጉ ተመርተው የኖሩ ደጋግ ሰዎች ናቸው:: ልጅ አጥተው መካን ሆነው ሲኖሩ ዘር እንዲሰጣቸው ወደ እግዚአብሔር ይጸልዩ ነበር:: እግዚአብሔርም  ጸሎታቸውን ሰምቶ ደም ግባቷ ያማረ መልከ መልካም የሆነች እንደ ጸሐይ የምታበራ ልጅ ሰጣቸው:: ቅድስት አርሴማ የነበረችበት ዘመን ዘመነ ሰማዕታት ይባላል:: ዲዮቅልጥያኖስ የሮም ቄሳር ሆኖ የነገሰበት (እኤአ ከ284ዓ/ም - 305 ዓ/ም) : አብያተ ክርስቲያናት የተዘጉበትና አብያተ ጣኦታት ተከፍተው ክርስቲያኖች በክርስቶስ ስም ልዩ ልዩ መከራና ሰማዕትነት የሚቀበሉበት ዘመን ነበር::  ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሴቶች ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤  ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ ከዚህም በላይ በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ፤  በድንጋይ ተወግረው ሞቱ፥ ተፈተኑ፥ በመጋዝ ተሰነጠቁ፥ በሰይፍ ተገድለው ሞቱ፥ ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ” እንዳለ  ዕብ  11:35-37
  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

Tewahedo የiPhone አፕ

ተዋሕዶ (Tewahedo) የተሰኘ የስልክ አፕ በማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ አይቲ ክፍል ተዘጋጅቶ ቀረበ:: ይህ የቤተክርስቲያን አገልግሎት ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን የቤተክርስቲያኒቷ ልጆች ሊያበረክቱ ለሚችሉት አገልግሎት ፋና ወጊ እንደሚሆን የታመንበት አፕ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች በጥቂቱ:-

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::

  ከጌታችንና ከአምላካችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ በፊት መስቀል የመቅጫ መሣሪያ ነበር። ሰውን በመስቀል ላይ መቅጣት የተጀመረውም በፋርስ ነው። ፋርስ የዛሬዋ ኢራን ናት። የፋርስ ሰዎች “ኦርሙዝድ” የተባለ “የመሬት አምላክ” ያመልኩ ነበር። ከዚህም የተነሣ “ወንጀለኛው ቅጣቱን በመሬት ላይ የተቀበለ እንደሆነ አምላካችን ይረክሳል፤” ብለው ስለሚያምኑ ወንጀለኛውን ከመሬት ከፍ አድርገው በመስቀል ላይ ይቀጡት ነበር። ይህም ቅጣት ቀስ በቀስ በሮማ ግዛት ሁሉ የተለመደ ሕግ ሆነ። ከዚህም ሌላ በኦሪቱ ሥርዓት ቅጣታቸውን በመስቀል ላይ የሚቀበሉ ሰዎች ርጉማንና ውጉዛን ነበሩ። ይህንንም እግዚአብሔር ለሙሴ “ማንም ሰው ለሞት የሚያበቃውን ኃጢአት ቢሠራ እንዲሞትም ቢፈረድበት፥ በእንጨትም ላይ ብትሰቅለው፥ በእንጨት ላይ የተሰቀለ በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና ሬሳው በእንጨት ላይ አይደር፤” ሲል ነግሮታል። ዘዳ.21፥22-23። እዚህ ላይ “በመስቀል ላይ ተሰቅሎ የሚሞት የተረገመ ከሆነ፥ ለምን ጌታችን በመስቀል ተሰቅሎ ሞተ?” እንል ይሆናል። ይህንንም እንደሚከተለው እናያለን።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ኅብረ ነገር

በስመ  አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ  አሐዱ አምላክ አሜን !

                           እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ አሸጋገራችሁ!

"የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አወጣለሁ::"
ሕዝ 36፥26

እግዚአብሔር አምላክ የሰውን ልጅ በእጆቹ አበጃጅቶ በአርአያው ከፈጠረው ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ የአባትነት ፍቅሩን ፣የፈጣሪነት ርኀራኄውን፣ የማያልቀውን ትዕግስቱን አላጓደለበትም:: ምክንያቱም እረኛችን ነውና በጎቹን፣ አምላካችን ነውና ፍጡሮቹን ፣ንጉሳችን ነውና ሕዝቦቹን አይተወንምና ነው።

ይሁንና የሰው ልጅ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ (በሮሜ 15፥20) ላይ እንደገለጸው "የማደርገውን አላውቅምና የምጠላውን ያን አደርጋለሁ፤ የምወደውን እርሱን አላደርገውም የማልወደውን ግን አደርጋለሁ። ፈቃድ አለኝና መልካሙን ግን ማድረግ የለኝም፤ የማልወደውን የማደርግ ከሆንኩ ግን ያን የማደርገው አሁን እኔ አይደለሁም በእኔ የሚኖር ኃጢያት ነው እንጂ። " በማለት የሰው ልጅ ዝንባሌ ከጽድቅ ይልቅ ኃጢያትን፣ ከሕይወት ይልቅ ሞትን፣ ከሰላም ይልቅ ሁከትን፣ ለአምላኩ ከመታዘዝ ይልቅ እንቢተኝነትን፣ እርስ በእርስ ከመፋቀር ይልቅ መጣላትን፣ ከአንድነት ይልቅ መለያየትን፣ ከመተሳሰብ ይልቅ ምቀኝነትን፣ ከቁም ነገር ይልቅ ቧልትን፣ ከመታመን ይልቅ አስመሳይነትን፣ ከእውነት ይልቅ ሐሰትን፣ ከሃይማኖተኛነት ይልቅ ከሃዲነትን እየመረጠ መላ ሕይወቱን እያናወጠ የሚጓዝ መሆኑን ያስገነዝበናል። ታዲያ የሰው ልጅ ማሰብ ሲገባው ከድካሙ ማስተዋል ሲኖርበት ከለገመ የድንጋይ ልብ አለው የሚባለው የዛን ጊዜ ነው።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ኅብረ ነገር

በመጋቤ ጥበብ በእምነት በቀለ

ጳጉሜን ፭ ቀን ፳፻፭ ዓ/ም.

                                      የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር

በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ዘመን የሚቆጠርበት ቀመር የሚቀመርበት ትምህርት ባሕረ ሐሳብ ይባላል። ባሕረ ሐሳብ ከሁለት የግእዝ ቃላት የተገኘ ነዉ። ባሕር ማለት በዘይቤ ሳይሆን በምስጢር ወይም በምሳሌው ዘመን ማለትን ያሰማል። “በመዳልው ደለወ ዓለመ ወበመስፈርት ሰፈራ ለባሕር” እንዲል። ባሕርን ሰፈራት ይላል ባሕር የሚሰፈር ሳይሆን ባሕርን ዘመን ለማለትና ዘመን በአዕዋዳት የሚታወድ፣ በቀመር የሚቀመር፣ የሚሰፈር መሆኑን ለማሳየት ነዉ። ሐሳብ ማለት ፍቺው ብዙ ቢሆንም እዚህ ላይ በአጭሩ ቁጥር ማለት ነው። “ኢትትሐሰብዎሙ ወርቆሙ ወብሩሮሙ ወለጽድቅከኒ አልቦቱ ሐሳብ - ለቸርነትህ ቁጥር ሥፍር የለውም” እንዲል አረጋዊ መንፈሳዊ፤ እንዲሁም ቅዱስ ዳዊት “ብፁዓን እለተኀድገ ሎሙ ኀጢአቶሙ ወእለኢሐሰበ ሎሙ ኩሎ ጌጋዮሙ - ኀጢአታቸዉ የተተወላቸው በደላቸው ያልተቆጠረባቸው ብፁዓን ናቸው” መዝ፤ 31፣1 ይላል። ስለዚህ ባሕረ ሐሳብ ማለት የዘመን አቆጣጠር ማለት ይሆናል። ሐሳበ ባሕርም ቢል ቁጥር ያለው ዘመን ማለት ነው።

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 8 of 41First   Previous   3  4  5  6  7  [8]  9  10  11  12  Next   Last   

 የ10 ዓመት የስብከተ ወንጌል ማስፋፋፊያ ፕሮጀክት Minimize

ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት እና ለመርዳት ይህንን ይጫኑ።


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ሶሻል ኔትወርኪንግ

Share |

  
 ግጻዌ


  
 የተላለፉ የቴሌቪዥን እና ሬዲዮ መርሃ ግብር ለመከታተል Minimize


  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement