View in English alphabet 
 | Tuesday, May 7, 2024 ..:: ኅብረ ነገር ::.. Register  Login
  

መንፈሳዊ ግብዣ

መንፈሳዊ ግብዣ


«ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።» /መዝ. ፻፴፫፥፩/

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን !

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሰ/ት/ቤ/ማ/መ ማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል የስብከተ ወንጌል መምህራንና ዘማርያን ጉባኤ ተሰናድቷል። የጉባኤው ዋና ዓላማ በሰሜን አሜሪካ እየተካሔደ ያለውን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ስለማጠናከርና በቅንጅትና በአንድነት መንፈስ ማገልገል ስለሚቻልበት ሁኔታ ለመመካከርና ልምድ ለመለዋወጥ ሲሆን በተጓዳኝ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ ጥናታዊ ጽሑፎች ይቀርባሉ። ውይይቶችም ይካሄዳሉ።

ስለዚህ እርስዎም በዚህ ዝግጅት ላይ እንዲሳተፉ በአክብሮት እንጋብዛለን።

ቀናት፦ ከሐሙስ ጥቅምት ፲፮ - ቅዳሜ ጥቅምት ፲፰ ቀን  ፳፻፬
Thursday, October 27, 2011 - Saturday, October 29, 2011
ቦታ፦ ኮሎምበስ፣ ኦሀዮ ደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ


«የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።» /፪ኛ ቆሮ. ፲፩፥፳፰/


Written By: admin
Date Posted: 9/29/2011
Number of Views: 4545

Return

  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement