ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን !
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሰ/ት/ቤ/ማ/መ ማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል የስብከተ ወንጌል መምህራንና ዘማርያን ጉባኤ ተሰናድቷል። የጉባኤው ዋና ዓላማ በሰሜን አሜሪካ እየተካሔደ ያለውን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ስለማጠናከርና በቅንጅትና በአንድነት መንፈስ ማገልገል ስለሚቻልበት ሁኔታ ለመመካከርና ልምድ ለመለዋወጥ ሲሆን በተጓዳኝ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ ጥናታዊ ጽሑፎች ይቀርባሉ። ውይይቶችም ይካሄዳሉ።
ስለዚህ እርስዎም በዚህ ዝግጅት ላይ እንዲሳተፉ በአክብሮት እንጋብዛለን።
ቀናት፦ ከሐሙስ ጥቅምት ፲፮ - ቅዳሜ ጥቅምት ፲፰ ቀን ፳፻፬
Thursday, October 27, 2011 - Saturday, October 29, 2011
ቦታ፦ ኮሎምበስ፣ ኦሀዮ ደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ
«የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።» /፪ኛ ቆሮ. ፲፩፥፳፰/