View in English alphabet 
 | Tuesday, April 23, 2024 ..:: ንቁ ::.. Register  Login
ንቁ

ሐዋርያዊት የሆነች ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን እውነተኛውን የክርስቶስን ወንጌለ መንግሥት ለ2000 ዓመታት በላይ ልጆቿ ስታውጅ እና ስታበስር ኖራለች:: በተለይም የራሷን ፓትርያርክ ሰይማ ከእራሷ ልጆች ኤጲስ ቆጶሳትን እየሾመች አገልግሎቷን መምራት ከጀመረችበት ጊዜ ጀምሮ በስብከተ ወንጌል እና አስተዳደር በኩል ተሰፋ ሰጪ ውጥኖች ታይተዋል:: ከውጪና ከውስጥ በሚነሱ ፈተናዎች ምክንያት የሚጠበቅባትን አመርቂ እርምጃ መራመድ ግን አልቻለችም::  በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ያሉ ምእመናንን በምግባር በሀይማኖት አጽንቶ ከበረት ውጭ ያሉትን የአፍሪካና የሌሎች አህጉራት በጎችን ወደ በረቱ ማምጣትና የተከታዩንም ቁጥር ከፍ ማድረግ ይጠበቅባታል:: ሆኖም ግን በተለይ ከ20 ዓመታት ወዲህ ተከስቶ ቀስ በቀስ እያደገ የመጣው እና እስከ መወጋገዝ ደረጃ ላይ የደረሰው የብፁዓን አባቶች ልዩነት የወቅቱ አውራ የቤተ ክርስቲያን ችግር ሆኖ በጉልህ ይታያል::

  ተጨማሪ ያንብቡ


ንቁ

“ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።” የማርቆስ ወንጌል 16፥15 

ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ በ ኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ በሰንበት  ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ከጳጉሜን 1985 ዓ. ም ጀምሮ ለ18ዓመታት በየወሩ አሁን ደግሞ በየሁለት ሳምንቱ  በመታተም የቤተክርስቲያንን ዜናዎችን፣ ትምህርተ ወንጌልን፣የአባቶችን ሕይወት፣ ከምዕመናን የሚነሱ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን ምላሽ በመስጠት፣ የገዳማት እና አድባራት እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶችን እንቅስቃሴ በመዘገብ ምዕመናን በማስተማር፣በማሳወቅ እና መንፈሳዊ ችግር/ፈተና ፈቺ በመሆን አገልግሎት ስትሰጥ የኖረች የቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ ነች::

ስምዐ ጽድቅ መታተም ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ ባቀረበቻቸው የቤተ ክርስቲያን ትምህርቶች የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት የሚጻረር ጽሁፍ አቅርባ አታውቅም:: ይህም የሆነበት ምክንያት ማንኛውም ጽሁፍ በጋዜጣዋ ላይ ከመውጣቱ በፊት ቅዱስ ሲኖዶስ ለማኅበሩ በሰጠው ስልጣን መሰረት ማኅበሩ ባቋቋመው የነገረ ሃይማኖት እና የጋዜጠኝነት ሙያ ጥልቅ ዕውቀት ባላቸው የኢዲቶሪያል ቦርድ አባላት ተደጋግሞ ስለሚገመገም ነው፣ በተጨማሪም የታወቁ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን  በነፃ ሓሳባቸውን እና ምክራቸውን በመለገስ ለማስተካከል ስለሚተባበሩ ነው::

  ተጨማሪ ያንብቡ


ንቁ

ኢትዮጵያ ያላት ክብርና ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ በተለያዩ የታሪክ ሰነዶች የተመሰከረ፣ በታላላቅ ማራኪ ቅርሶችም የታጀበ ነው። የነበራት ክብርና ገናናነት ከምዕራብ እስከ ምስራቅ፣ ከሰሜንም እስከ ደቡብ የታወቀ ነው። ከዚህ ጉልህ ታሪክ ውስጥ የበለጠ ጎልቶ የሚታየው ደግሞ የሀገራችን የሃይማኖት ታሪክ ነው። ኢትዮጵያ ከእስራኤል ወገን ቀጥሎ ብሉይ ኪዳንን በመቀበል ቀዳሚ ሀገር ናት። በመሆኑም በዘመነ ብሉይ ሕግና ነቢያትን በመቀበልና በመፈጸም እንዲሁም የተስፋውን ቃል በመጠበቅ ኖራለች። ጊዜው ሲደርስም የሐዋርያትን ስብከት ተቀብላ የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነትና ጌትነት አምና ጥምቀትን ወደ ምድሯ አምጥታለች። በመሆኑም ወንጌልን ተቀብላ አምና ስትሰብክ ኖራለች። አሕዛብ ሕግና ነብያትን በናቁበት ጊዜ ከአሕዛብ ወገን ቀድማ ከእስራኤል ሕዝብ ጋር ኦሪትን በመቀበሏ እንዲሁም ደግሞ እስራኤል ወንጌልን በናቁበት፣ ክርስቶስን በጠሉበት ጊዜ ከአሕዛብ ጋር ሐዲስ ኪዳንን በጊዜው በመቀበሏ ሁለቱንም ኪዳናት በጊዜያቸው ያስተናገደች ብቸኛ ሀገር ናት ማለት ይቻላል። ስለዚህ በዓለምም ሆነ በአፍሪካ መድረክ የሚያስከብር የሃይማኖት ታሪክ ባለቤት ናት። ከዚያም በመነጨ ሊሻሩ ከማይችሉት ከሕግና ከነቢያት እንዲሁም ከክርስቶስ ወንጌል፣ ከሐዋርያት ትምህርት፣ ከሊቃውንቱም ትርጓሜ የመነጨ ሰውንም እግዚአብሔርንም ደስ የሚያሰኝ ሥርዓተ አምልኮ ባለቤት ለመሆን አስችሏታል።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ንቁ

(አዲስ አበባ)፡- ዕለተ ዓርብ መስከረም 30/2001 ዓ.ም ነው፡፡ ሰዓቱም ከጠዋቱ 2 ሰዓት፡፡ እንደተለመደው ሃይማኖታዊ ተግባር ሁሉ በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ (አራዳ ጊዮርጊስ) ቤተ ክርስቲያን ኪዳን ከተደረሰ በኋላ ምእመናን ወደየቤታቸው ሊሄዱ ሲዘጋጁ ነበር፤ ከቤተመቅደሱ አቅራቢያ ያልተለመደ አስደንጋጭ ድምፅ የተሰማው፡፡


ከነጫማው ወደ ቤተ ክርስቲያን የገባ አንድ ግለሰብ ወለል ላይ ነጠላ አንጥፎ የሙስሊም የእምነት ሥርዓት በሚመስል መልኩ እየሰገደ «አላህ ወአክባር፣ አላህወአክባር፣ ሥዕል ይውረድ፣ መስኪድ ይሠራ .. አላህወአክባር» እያለ ይጮሃል፡፡ ባልተለመደው ክስተት የተደናገጡት ምእመናን ዝም አላሉም ግለሰቡን ይዘው የደብሩን ጥበቃ ሠራተኛ ጠርተው ከቤተ መቅደስ እንዲወጣ አደረጉት፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ



Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement