View in English alphabet 
 | Friday, July 26, 2024 ..:: ስብከተ ወንጌል ::.. Register  Login
ስብከተ ወንጌል

አንድ ሶርያዊ ክርስቲያን የሚከተለውን ደብዳቤ በ1983 .ም ጽፎ ነበር፡፡ ደብዳቤው እንዲህ ይነበባል፡-

«እስከ 1970 .(የተወለደው በ1943 .ም ነው) «በቤተ ክርስቲያን ትምህርት መሠረት ሥጋ ወደሙ እቀበል ነበር፣ አሥራት አወጣ ነበር፣ ገዳማትን ለመርዳት የተቋቋመ ማኅበር አባል ሆኜ ሌት ተቀን እሠራ ነበር፣ ሁል ጊዜ በመንፈሳዊ ሕይወቴ ውስጥ የመለወጥ ስሜት ነበረኝ፣ ለመማር፣ ለመጾምና ለመጸለይ የነበረኝን ትጋት አስታውሰዋለሁ፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

አንድ ሶርያዊ ክርስቲያን የሚከተለውን ደብዳቤ በ1983 ዓ.ም ጽፎ ነበር፡፡ ደብዳቤው እንዲህ ይነበባል፡-

«እስከ 1970 ዓ.ም (የተወለደው በ1943 ዓ.ም ነው) «በቤተ ክርስቲያን ትምህርት መሠረት ሥጋ ወደሙ እቀበል ነበር፣ አሥራት አወጣ ነበር፣ ገዳማትን ለመርዳት የተቋቋመ ማኅበር አባል ሆኜ ሌት ተቀን እሠራ ነበር፣ ሁል ጊዜ በመንፈሳዊ ሕይወቴ ውስጥ የመለወጥ ስሜት ነበረኝ፣ ለመማር፣ ለመጾምና ለመጸለይ የነበረኝን ትጋት አስታውሰዋለሁ፡፡
  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን




ቤተልሔም እንሂድ ሉቃ ፪፥፲፭

በመልአከ ሕይወት ቀሲስ ዕርገተቃል ይልማ

ቤተልሔም ማለት የእንጀራ ቤት ማለት ነው። ታሪካዊ ሥፍራ ናት። ዳዊትም ተወልዶ ያደገው፣ ለንጉሥነት የተቀባውና ቤተ መንግሥቱም የነበረው በቤተልሔም ነበር። ስለዚህ በእስራኤላዊያን ታሪክ ውስጥ ቤተልሔም የተወለደ «ቤተልሔማዊ ነኝ» ብሎ ራስን ማስተዋወቅ ክብር ነበረው።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

“ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም”

እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሳ መዝ( ፸፯÷፷፭)

በቀሲስ አድማሴ መኮንን

 

በትራክት መልክ የተዘጋጀውን ለማግኘት ይህንን ይጫኑ።

ታላቁ አባት ቅዱስ ኤፍሬም ሃይማኖተ አበው በተባለው መጽሐፍ ምዕራፍ ፵፯ ክፍል ፩ ቁጥር ፮ ላይ ልዩ በሚሆን ድንቅ በሚያሰኝ መለወጥ ይስማማው በነበረ ሥጋ በተወለደው ልደት ወደ አልተለመደው ነገር /ወደ ሞት/  ወደ መስቀል ደረሰ ( ኢሣ ፱÷፮ _ ፯)::  እኛን የሚመስል ሥጋን ገንዘብ አደረገ ይኸውም ከሁሉ ጋራ አንድ ነው ከባህርያችን የተገኘው አንድ አካል አንድ ባህርይ የሆነ እርሱ ሕማም ሞት የሌለበት ሲሆን በሥጋ ባህርይ ኃጥያት ሳይኖርበት ታመመ ሞተ እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጥያት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጥአት አደረግነው(፪ኛቆሮ ፭÷፳፩)“ በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ ኃሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሣለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማትን እንደሚገባ ነገር አልቆጠረውም ነገር ግን የባርያውን መለክ ይዞ በሰው ምሣሌ ሆኖ ራሱን ዝቅ አደረገ በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ “(ፊልጵ፪÷፭ _ ፱)“

  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

«አንች የጽዮን ልጅ አትፍሪ፤ እነሆ ንጉሥሽ በእህያ ውርንጫ ላይ ተቀምጦ ይመጣል» ተብሎ እንደተጻፈ ኢየሱስ የአህያ ውርንጫ አግኝቶ በእርሱ ተቀመጠ ዮሐ.12፥15፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከመምጣቱ አስቀድሞ 1400 ዓመታት በፊት እግዚአብሔር በአብርሃም የእምነት ቃል ኪዳን ሕዝቡ ያደረጋቸውን እስራኤላውያንን በጽኑ  ክንድ ከባርነት ቀንበር አውጠቶ ቀን በደመና ሌሊት በብርሃን አምድ እየመራ በመገናኛዋ ድንኳን ውስጥ አድሮ እርሱ ንጉሣቸው ሆኖ እነርሱ ደግሞ ህዝቡ ሆነው በምድረ በዳ መራቸው፤ ወደ ተስፋይቱ ምድር ከነዓንም አገባቸው፡፡ እስራኤል ግን ምድራዊ ንጉሥ በመፈለግ ንጉሣቸው እግዚአብሔርን በመተዋቸው እግዚአብሔርን በደሉ፤ በምድር ላይ ያለች የመንግሥቱ ማሳያ ሊሆኑ የመረጣቸው ሕዝቡ ምድራዊ ንጉሥ ፈልገዋልና፡፡ መልከ መልካምና ያማረ የሆነው ሳኦል እስራኤል የመረጡት ምድራዊ ንጉሥ ውጫዊ ክብር ብቻ ያለው መሆኑን አስመስከረ፡፡ እግዚአብሔር ግን ከዚህ ዓለም ያልሆነች በቁሳዊው ኅብር ያላጌጠች፣ የትህትናና የፍቅር የምሥጋና የሆነች መንግሥቱን ሊያመለክት ሲወድ ከወንድሞቹ ሁሉ ያነሰውንና በገና ደርደሪውን የእሴይን ልጅ ዳዊትን መረጠ፡፡ የዳዊት መንግሥት ብታልፍም « ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አስቀምጣለሁ» ያለውን ቃልኪዳን ግን አላጠፋም ፡፡ ስለዚህም በአምላክነቱ ለዘላለም የነገሥታት ንጉሥ የሆነ ወልድ ከዳዊት ዘር ሰው ሲሆን የዳዊት ተስፋ ተፈጸመ፤ በመለኮታዊ ስልጣኑ በእግዚአብሔር እሪና ያለው ወልደ እግዚአብሔር የዳዊት ልጅ ሆኗልና፡፡

ሉውን ማንበብ ይህን ይ
  


Page 2 of 6First   Previous   1  [2]  3  4  5  6  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement