View in English alphabet 
 | Friday, April 26, 2024 ..:: ስብከተ ወንጌል ::.. Register  Login
ስብከተ ወንጌል

ቆሮንቶስ የግሪክ ከተማ ናት። ከአቴናም 75 ኪ.ሜ. ያህል ትርቃለች። በአዲስ ኪዳን ዘመን ስድስት መቶ ሺህ ሰዎች የሚኖሩባት ትልቅ ከተማ ነበረች። አቀማመጧ በሁለቱ የግሪክ አውራጃዎች በመቄዶንያና በአካይያ መካከል በሚገኘው ልሳነ ምድር ነበረ።

ከተማይቱ የተመሠረተችው በባሕር መገናኛ ላይ በመሆኑ ከምሥራቅና ከምዕራብ ለሚመጡ መርከቦች ምቹ ወደብ ነበረች። ከዚህም የተነሣ ንግድ እየደራባት ሄደ። ከተማይቱም እጅግ ተለወጠች። የከተማይቱ ነዋሪዎች የሚያመልኩት አፍሮዳይቲ የምትባለዋን የፍቅር አምላክ ነበር። «ቆሮንቶሳዊ» መባል የስድብ ስም እስኪሆን ድረስ የዝሙት ኃጢአት በከተማይቱ በዛ። አብዛኛዎቹ ነዋሪዎች ግሪኮች ሲሆኑ ብዙ ሮማውያንና አይሁዶች ይኖሩባት ነበር።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

ማንም ሲፈተን በእግዚአብሔር እፈተናለሁ አይበል
/በቀሲስ ዶ/ር መስፍን ተገኝ/

  


ስብከተ ወንጌል

የሚበላውም የማይበላውን አይናቀው፤ የማይበላውም የሚበላውን አይንቀፈው
/በመልአከ ሰላም ደጀኔ ሽፈራው/

  


ስብከተ ወንጌል

በመላከ ሕይወት ቀሲስ ዕርገተቃል ይልማ

ትራክቱን ለማግኘት ይህን ይጫኑ

ቤተልሔም ማለት የእንጀራ ቤት ማለት ነው። ታሪካዊ ሥፍራ ናት። ዳዊትም ተወልዶ ያደገው፣ ለንጉሥነት የተቀባውና ቤተ መንግሥቱም የነበረው በቤተልሔም ነበር። ስለዚህ በእስራኤላዊያን ታሪክ ውስጥ ቤተልሔም የተወለደ «ቤተልሔማዊ ነኝ» ብሎ ራስን ማስተዋወቅ ክብር ነበረው። ቤተልሔም የእስራኤል መንግሥት ለሁለት ሲከፈል ቀድሞ የነበራት ታላቅነትና ዝና እንዳልነበረ ሆኗል። ከነቢያት ወገን የሆነው ሚክያስ ለማስተማር ሲያልፍ ይቺ ስመ ጥር የሆነችው ከተማ ተፈትታ፣ ምድረ በዳ ሆና፣ ቋያ በቅሎባት ክብሯ ሁሉ ከላይዋ ላይ ተገፎ ተመለከታት። ከተማይቱ እንደዚህ ሆና እንደማትቀር በመንፈስ ቅዱስ ተረድቶ «አንቺ ቤተልሔም ኤፍራታ ሆይ የይሁዳ ምድር፣ ከይሁዳ ገዥዎች ከቶ አታንሽም ሕዝቤን እስራኤልን የሚጠብቅ መስፍን ከአንቺ ይወጣልና» ሚክ ፭፥፪ ሲል ተነበየላት።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

በዲ/ን አብነት አረጋ


“በቸርነትህ ዓመት ታቀዳጃለህ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል ኮረብቶች በደስታ ይታጠቃሉ። ማሠማሪያዎችም መንጎችን ለበሱ ሸለቆዎችም በእህል ተሸፈኑ በደስታ ይጮኻሉ ይዘምሩማል”  /መዝ ፷፬(፷፭)፥፲፩-፲፫/
እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ በሰላም አሸጋገርዎ!
  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 4 of 6First   Previous   1  2  3  [4]  5  6  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement