View in English alphabet 
 | Friday, April 26, 2024 ..:: ነገረ ቅዱሳን ::.. Register  Login
ነገረ ቅዱሳን

ቅዱሳን መላእክት በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ለአገልግሎት የሚፋጠኑ ናቸው፡፡ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትንና ቸርነትን ወደ ሰው ልጆች፣ የሰዎችንም ጸሎትና ልመና ወደ እግዚአብሔር የሚያደርሱ ናቸው፡፡

ስለ ተራዳኢነታቸው - በቅዱሳት መጻሕፍት

ቅዱሳን መላእክት በመንገዳችን ሁሉ እንደሚጠብቁን ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ሲያስረዳ እንዲህ ብሏል «በመንገድ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንነተ ያዝዛቸዋልና፣ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል» (መዝ. 90/91/-11)፡፡
  ተጨማሪ ያንብቡ


ነገረ ቅዱሳን

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ሃያ ስድስት በዚህች ቀን የከበረ ሞይስስና እኅቱ ሣራ በሰማዕትነት ያረፉበት ነው።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተራራው ስብከቱ “መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፤ ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል፤ መልካም ዛፍ ክፉ ፍሬ ማፍራት አይቻለውም” በማለት እንዳስተማረ የእሊህም ቅዱሳን ወላጆቻቸው መልካም ፍሬን እንዳፈራው ዛፍ ደጎችና እጅግም ባለጸጎች ነበሩ። /ማቴ. ፯፥፲፯-፲፰/
  ተጨማሪ ያንብቡ


ነገረ ቅዱሳን

ብዙውን ጊዜ “ጠቢቡ” የሚለው ቃል ይቀጸልለታል። በእርግጥም በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ንጉሥ ሆኖ በተሾመ ጊዜ በፍጹም አትኅቶ (ራስን ዝቅ በማድረግ) “መልካሙንና ክፉውን ይለይ ዘንድ ለባሪያህ አስተዋይ ልቡናን ስጠው” በማለት ከብርና ከወርቅ ይልቅ የበለጠውን ነገር በመለመኑ እግዚአብሔር ተደሰተበት። “እኔ እንደቃልህ አድርጌልሀለሁ እነሆ ማንም የሚመስልህ ከአንተ በፊት እንደሌለ ከአንተም በኋላ እንዳይነሳ አድርጌ ጥበበኛና አስተዋይ ልቡና ሰጥቼሀለሁ” ተባለ። /፩ ነገ. ፫፥፱-፲፬/ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ከ፲፻፲፱-፱፻፸፱ ዓ.ዓ. የነገሠው ሰሎሞን።

ሰሎሞን እጅግ በጣም በጥበብና ልብን በሚነኩ ምሳሌዎች የተሞሉ አምስት መጻሕፍትን ደርሷል። ከእነዚህ ውስጥ አንዱ “መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን” ይባላል። ከመዝሙራት ሁሉ የሚበልጥ መዝሙር እንደማለት ነው። በዚህ መጽሐፍ እግዚአብሔር አምላካችን በገለጠለት መጠን በሴት አንቀጽ እየጠራና በፍቅር እየመሰለ ስለሐዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያንና ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ብዙ ምሥጢር ተናግሮበታል።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ነገረ ቅዱሳን

ባለፈው የሁለተኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ ሰማዕቱ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ዜና ሕይወትና ሰማዕትነት እንዴት እንደ ተቀበሉ ተመልክተናል። አሁን ደግሞ ከቅዱስነታቸው 43 ዓመታት በፊት በፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል የሰማዕትነት አክሊል የተቀዳጁትን የሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቀዳማዊ ዜና ሕይወትና የሰማዕትነት ታሪክ እናቀርባለን።

በ1875 ዓ.ም. በሰሜን ሸዋ አገረ ስብከት ሰላሌ አውራጃ ፍቼ ከተማ ተወለዱ። ወላጆቻቸው ዕድሜያቸው ገና በወግ ለትምህርት ሳይደርስ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመውሰድ ባሕታዊ ተድላ ለተባሉ መምህር አደራ ሰጧቸው። በዚያው ገዳም የንባብ ቤቱንና የዜማውን የትምህርት ደረጃዎች በሚያስገርም ሁኔታ በአጭር ጊዜ አቀላጥፈው በመጨረስ ገና በልጅነት የዕድሜ ደረጃቸው ሦስተኛውን የቅኔ ትምህርት ጀምረው በአጭር ጊዜ ሙሉ ቤት ተቀኙ። ይህንኑ የቅኔ ትምህርት ለማስፋፋት በምዕራብ ጎጃም አገረ ስብከት ወደሚገኘው የቅኔ ትምህርት ማዕከል ዋሸራ ተሻግረው ለመምህርነት የሚያበቃውን ትምህርት ፈጽመው አስመሰከሩ።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ነገረ ቅዱሳን

ይህች ቅድስት ከኒቆምድያ ሀገር በሐዋርያው በቅዱስ ጳውሎስ ዘመን ሐዋርያዊት የሆነች ናት። ቅዱስ ጳውሎስም ከአንጾኪያ ከተማ በወጣ ጊዜ፤ ወደ ኒቆምድያ ከተማ ሄደ። በዚያም ስሙ ስፋሮስ የሚባል ምዕመን ሰው ነበር። ቅዱስ ጳውሎስን ወስዶ በቤቱ አኖረው፤ ብዙ አሕዛብም የሐዋርያው የጳውሎስን ትምህርት ይሰሙ ዘንድ በእርሱ ዘንድ ይሰበሰቡ ነበር።

ይህች ቅድስት ቴክላም በቤቷ መስኮት ተመለከተች፤ የሐዋርያውንም ትምህርት ሰማች። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን “ፈታኝ ቀርቦ፤ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ እነዚህን ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው። እርሱም መልሶ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ፤ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፏል።” ብሎ እንደመለሰለት እንዲሁም ትምህርቱን እያዳመጠች ሳትበላና ሳትጠጣ ሦስት ቀኖች ቆየች። ትምህርቱም በልቧ አደረ፤ አባትና እናቷ ቤተሰቦቿም ሁሉ አዘኑ። ከምክርዋም እንድትመለስ ሐዋርያው ጳውሎስንም እንዳትከተል ለመኗት፤ ነገር ግን አልሰማቻቸውም። /ማቴ. ፬፥፫-፬/።
  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 3 of 5First   Previous   1  2  [3]  4  5  Next   Last   

Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement