View in English alphabet 
 | Friday, April 26, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
አማርኛ




ላክ   ተወው
ዜና

በዝቋላ እየተካሄደ ላለው የእሳት ማጥፋት እንቅስቃሴ ርዳታ በማድረግ ላይ ላላችሁ በሙሉ

Zekuala Fireማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል፣ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ እና ማኅበረ በዓለ ወልድ በአንድነት እያስተባበሩት ባሉት እና ዓላማው በአሁኑ ወቅት እሳቱን ለማጥፋት ከየአካባቢው በነቂስ ለወጣው ኢትዮጵያዊ ወገናችን ጉሮሮውን ማርጠቢያ ውኃ፣ ጉልበቱን መደገፊያ ዳቦ ማቅረቢያ እንዲሆን እንዲሁም በገዳሙ ጥሪታቸውን አሟጠው እንግዶቻቸው እሳት ተከላካዮችን  በማስተናገድ  ላሉት ገዳማውያን ርዳታ ማድረግ በሆነው ታላቅ እንቅስቃሴ እስካሁን በፔይፓል (http://zekuala.mahiberekidusan.org/) አካውንታችን (ይህ ጽሑፍ በተዘጋጀበት ወቅት) ሁለት መቶ ሰላሳ ወንድሞች እና እህቶች በዚህ የአጭር ጊዜ አፋጣኝ ጥሪ ምላሽ ሰጥተዋል። ሌሎችም በመለገስ ላይ ይገኛሉ። እናመሰግናለን።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

 

በዝቋላ ገዳም እና አካባቢው ደን ላይ የተነሣውን እሳት ለማጥፋት ለሚደረገው ጥረት የግል ልገሳዎን ይስጡ በሚል ሐሳብ በማ/ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል፣ በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ እና በማኅበረ በዓለ ወልድ አስተባባሪነት በሰሜን አሜሪካ የምንገኝ ኦርቶዶክሳውያን አስቸኳይ የገንዘብ ማሰባሰብ ሒደት ላይ እንገኛለን። ዓላማው በአሁኑ ወቅት እሳቱን ለማጥፋት ከየአካባቢው በነቂስ ለወጣው ኢትዮጵያዊ ወገናችን ጉሮሮውን ማርጠቢያ ውኃ፣ ጉልበቱን መደገፊያ ዳቦ ማቅረቢያ እንዲሆን የታሰበ ነው። በባዶ እጁ፣ በቅጠል እና በአፈር ቋያ እሳት ለማጥፋት እየታገለ ላለው ወገን አለኝታነታችንን ለመግለጽ ነው። ስለዚህም በሚከተለው አድራሻ እየገባችሁ የግላችሁን ልገሳ መስጠት የምትችሉ መሆኑን በትህትና እናስታውቃለን።
http://zekuala.mahiberekidusan.org/
  


ትምህርተ ሃይማኖት

ንስሐ የግዕዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙ ጸጸት ነው፡፡ ጸጸትነቱ ሰው በሠራው ኃጢአት ተጸጽቶ ኃጢአቱ ይሰረይለት ዘንድ እግዚአብሔርን በሐዘን በለቅሶ ሲለምን እንጂ የጐልማሳ ሚስት ሳልቀማ፣ የሰው ገንዘብ ሳልሰርቅ ቀረሁ … በማለት የሚጸጸተው ጸጸት አይደለም፡፡


ንስሐ ለተጠመቁ ሰዎች ከጥምቀት በኋላ የተሰጠች ሀብት ናት። በጥምቀት ከእግዚአብሔር የምትገኝ የልጅነት ሁለተኛ ማዕረግ ናት፡፡ በሃይማኖት ገንዘብ ያደረግነው የመንግሥተ ሰማያት አራቦን ማለትም መግዣ ናት። ንስሐ ለሚሿት ሰዎች የተከፈተች የይቅርታ በር ናት፡፡ በንስሐ በርነት ከፈጣሪ ወደሚገኝ ቸርነት እንቀርባለን።

ምሥጢረ ንስሐ ማለት አንድ ሰው ከጥምቀት በኋላ የፈጸመውን ጥፋት አውቆ ሁለተኛ ጥፋቱን ላለመድገም ወስኖ በእግዚአብሔርና በካህኑ ፊት ተንበርክኮ ከልቡ ተጸጽቶ ኃጢአቱን በመናዘዝ ከኃጢአቱ እስራት የሚፈታበትና ከእግዚአብሔር ይቅርታን የሚያገኝበት ታላቅ የይቅርታ ምሥጢር ነው።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

መጋቢት 12/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

 


ከሥፍራው በደረሰን መረጃ መሠረት ምእመናን የመዳከም ሁኔታ የሚታይባቸው ሲሆን የአዳማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ሌሎችም ምእመናን ደየመጡበት በመመለስ ላይ ናቸው፡፡ የፌደራል ፓሊስና የኦሮሚያ ፖሊስ ከቀሩት ምእመናን ጋር በመሆን የሚጨሰውን ፍም በማጥፋት ሥራ ላይ ተጠምደዋል፡፡ ወደ ዝቋላ ገዳም ከተለያዩ አቅጣጫዎች ምእመናን እየሔዱ ሲሆን በሥፍራው የሚገኙ ምእመናን አሁንም ተጨማሪ የሰው ኀይል እንዲደርስላቸው በመጠየቅ ላይ ናቸው፡፡

  


ስብከተ ወንጌል

የሚበላውም የማይበላውን አይናቀው፤ የማይበላውም የሚበላውን አይንቀፈው
/በመልአከ ሰላም ደጀኔ ሽፈራው/

  


Page 18 of 41First   Previous   13  14  15  16  17  [18]  19  20  21  22  Next   Last   

 የ10 ዓመት የስብከተ ወንጌል ማስፋፋፊያ ፕሮጀክት Minimize

ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት እና ለመርዳት ይህንን ይጫኑ።


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ሶሻል ኔትወርኪንግ

Share |

  
 ግጻዌ


  
 የተላለፉ የቴሌቪዥን እና ሬዲዮ መርሃ ግብር ለመከታተል Minimize


  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement