View in English alphabet 
 | Friday, April 26, 2024 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
አማርኛ




ላክ   ተወው
ክርስቲያናዊ ሕይወት, ትምህርተ ሃይማኖት

የምሥጢረ ቁርባን አመሠራረት
ምሥጢረ ቁርባንን ጌታችን ከሕማማቱና ከሞቱ በፊት በዋዜማው ኀሙስ ማታ መሥርቷል። ይህም ሰዓት በአይሁድ የቀን አቆጣጠር ወደ ዓርብ ይታሰባል። በዚያም ወቅት የኦሪት የፋሲካ በግ የሚሠዋበት ጊዜ በመሆኑ ጌታችን ከደቀመዛሙርቱ ጋር የኦሪትን መሥዋዕት አሳልፎ መሥዋዕተ ወንጌልን መሥርቷል። በዚያችም ምሽት የኦሪቱን በግ መሥዋዕትነት አበቃ፤ ከእንግዲህ ወዲህ እውነተኛው የእግዚአብሔር በግ ይሠዋል። እርሱም የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው። ስለዚህ በማዕዱ ዙሪያ ለተሰበሰቡት ሐዋርያቱ በብሉይ ኪዳን ምሳሌ የተመሰለለትን: ትንቢት የተነገረለትን አዲሱን ቃል ኪዳን ጌታ በራሱ ሥጋና ደም መሠረተ። የእውነተኛው መሥዋዕት ምሳሌ የሆነው የኦሪቱን ማዕድ እየበሉ ሳለ “ኢየሱስ እንጀራና ኅብስትን አንስቶ ባረከ ቆርሶ ለደቀመዛሙርቱ ሰጠና እንካቹ ብሉ፤ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ ሁላችሁም ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው” በማለት ምሥጢረ ቁርባንን መሠረተ /ማቴ ፳፮፣፳፮-፳፰/። ኪዳን ማለት ከእግዚአብሔር ጋር የምንገባው ቃል ኪዳን የሚያመለክት ነው።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ክርስቲያናዊ ሕይወት, ትምህርተ ሃይማኖት

ምሥጢረ ቁርባን ማለት ክርስቶስ ስለ እኛ ኃጢአት በመስቀል ላይ መሥዋዕት ሆኖ በሥጋው በመሞቱ የዓለምን ኃጢአት ያስወገደበት፣ የዘላለም ሕይወትን ያሰገኘበት፣ የመዳናችን መሠረት፣ የጸጋችን ሁሉ ምንጭ የሆነውን የቅዱስ ሥጋውንና የክቡር ደሙን የማዳን ጸጋ የሚያመለክት ታላቅ የክርስትና ሃይማኖት ምሥጢር ነው። ክርስቶስ እንደ መሥዋዕትም እንደ ዐቢይ ሊቀ ካህናትም በመሆን ሁለቱንም በአንድ ጊዜ ፈጽሟል (ዕብ ፯፣፳፡፳፰)። እንደ ዐቢይ ሊቀ ካህናትነቱ በመስቀል ላይ የተቆረሰው ሥጋውን የፈሰሰው ደሙን የኃጢአት መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር በማቅረቡ ሰውን ከራሱና ከእግዚአብሔር ጋር አስታራቀ፣ የጥልንም ግድግዳ አፈረሰ፣ የተራራቀውን አቀራረበ።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

                 “የ፭ቱ ታቦታት የቀይ ምንጣፍ ጉዞ” በሲያትል ከተማ

በሰሜን ምዕራብ አሜሪካ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሲያትል ከተማ የሚገኙት አምስት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ማለትም የደብረ መድኃኒት ቅዱስ አማኑኤል ወአቡነ አረጋዊ ፤ የደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ፤ የደብረ ቁስቋም ቅድስት ማርያም ወደብረ ቀራንዮ መድኃኔዓለም ፤ የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል እና የደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት አብያተ ክርስቲያናት የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ጥምቀት ከሁለት ሺህ በላይ ምዕመናን በተገኙበት ጥር ፲  እና ፲፩ ቀን ፳፻፮ ዓ/ም (January 18/19 2014) በታላቅ ድምቀት አከበሩ::

  ተጨማሪ ያንብቡ


ትምህርተ ሃይማኖት

በትራክት መልክ የተዘጋጀውን የአማርኛ የጥምቀት መልእክት እዚህ ያግኙ
Find the English Epiphany message in a tract form here


የጥምቀት አስፈላጊነት

በቀሲስ ብርሃኑ ጎበና



በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከኒቂያ ጉባኤ በኋላ ከተነሱት አባቶች አንዱ “በፊተኛው ትንሣኤ ዕድል ያለው ብፁዕና ቅዱስ ነው ሁለተኛው ሞት በእነርሱ ላይ ሥልጣን የለውም” ራእይ ፳፥፮ የሚለውን የወንጌላዊው ዮሐንስን አባባል በተረጎመበት የእግዚአብሔር ከተማ በሚለው መጽሐፉ ላይ ፊተኛው ትንሣኤ የተባለው ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና የምናገኝበት ጥምቀት እንደሆነ ገልጿል (De Civitate Dei,xx,6)።
  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን




ቤተልሔም እንሂድ ሉቃ ፪፥፲፭

በመልአከ ሕይወት ቀሲስ ዕርገተቃል ይልማ

ቤተልሔም ማለት የእንጀራ ቤት ማለት ነው። ታሪካዊ ሥፍራ ናት። ዳዊትም ተወልዶ ያደገው፣ ለንጉሥነት የተቀባውና ቤተ መንግሥቱም የነበረው በቤተልሔም ነበር። ስለዚህ በእስራኤላዊያን ታሪክ ውስጥ ቤተልሔም የተወለደ «ቤተልሔማዊ ነኝ» ብሎ ራስን ማስተዋወቅ ክብር ነበረው።
  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 6 of 41First   Previous   1  2  3  4  5  [6]  7  8  9  10  Next   Last   

 የ10 ዓመት የስብከተ ወንጌል ማስፋፋፊያ ፕሮጀክት Minimize

ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት እና ለመርዳት ይህንን ይጫኑ።


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ሶሻል ኔትወርኪንግ

Share |

  
 ግጻዌ


  
 የተላለፉ የቴሌቪዥን እና ሬዲዮ መርሃ ግብር ለመከታተል Minimize


  
Copyright 2016 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement